2017 ጁን 18, እሑድ

የትግራይ ሕዝብ ትናንት ታግዬ አታግዬ ለወገኖቼም ድጋፍ ሰጥቼ የተለየ ጥቅም ይገባኛል አላለም

https://www.facebook.com/TG Onorham

********* amazing-speech **********

የትግራይ ሕዝብ ትናንት ታግዬ አታግዬ ለወገኖቼም ድጋፍ ሰጥቼ የተለየ ጥቅም ይገባኛል አላለም

የትግራይ ሕዝብ ከፍተኛ አስተዋፅኦ አድርገዋል ይሁን እንጂ ከፍተኛ ጥቅም ይገባኛል አላለም።

ሰሞኑን ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ከተለያዩ የመንግስት እና የፓርቲ የስራ ሃላፊዎች ጋር በወቅታዊ ሁኔታዎች ዙሪ ያ ውይይት አካሂዶ ነበር .. በውይይት ተካፋይ ከነበሩት አንዱ የሆኑት የት\ት ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ጸረ ህዝብ ሃይሎች አለ ስለሚሉት እና ለፕሮፖጋንዳ ግብአትነት እያዋሉ ሰለሚገኙት የህወሃት የበላይነት በተመለከተ ለተጠየቁት ጥያቄ የሰጡትን ምላሽ ..ቃል በቃል ወደጽሁፍ ቀይረን እንዲህ አቅርበነዋል 
...................................................................
« ሃገሪቱ ምን ታመነጫለች ለማን ምን እንስጥ ተብሎ በፍትሃዊ በሆነ ቀመር እንደሚሰራ አውቃለሁ ህያው ምስክር ነኝ ስለዚህ በዚህ በኩልም በመንግስት ስልጣን የማንንም ብሄር የበላይነት የሚያሳይ ምንም ነገር የለም 
እነሱ በስም የሚያነሱት የትግራይ ህዝብም ሆነ ህወሃትን ወስደን በምንመለከትበት ጊዜ በህገ መንግስቱም ሆነ በፓርቲ አስራራችን ውስጥ ህወሃት የበላይነት የለውም የህወሃትን የበላይነት ወይንም በኢትዮጵያ ህገመንግስት ውስጥ የትግራይን ህዝብ የበላይነት የሚያሳይ ምንም ነገር የለም እንደማንኛውም ህዝቦችና ድርጀት የራሳቸው ተገቢና አስፈላጊ ስፍራ አላቸው ታድያ ይህ ከሆነ ለምንድነው እነዚህ የትምክህትና የጥበት ሃይሎች የበላይነት ያለ አስመስለው የሚስሉት እና የሚጠሉት ተብሎ ሲታይ ሁለት ነገር በደንብ መታየት አለበት አንደኛ አሁን ኢትዮጵያ ውስጥ የመጣውን ለውጥ በመምራት እና በማስተባበር መነሻ የነበረው ህወሃት ነው ህወሃትንም ያፈለቀው የትግራይ ህዝብ ነው ትግሉ በተደረጀና በተቀናጀ መንገድ በአንድ አላማ ዙሪያ እንዲካሄድ የተደረገበት ቦታ ቢኖር የትግራይ ህዝቦች ናቸው ለዚህ አስተዋጽኦ ያደረጉት በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ታጋዮች የህይወትና የአካል መስዋት አድርገዋል ከፍለዋል እነዚህ ታጋዮች በዚህ አካባቢ ይህን ለውጥ የሚያመጣ አላማ ሲቀርጹና ለለሎች የሃገራችን ብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች አብዮታውያን ሃይሎች ሃሳባቸውን ሲያጋሩ አቅፈው ደግፈው ይዘው ልጆቻቸውን አዋተው ደም ከፍለው ህይወት ገብረው ትግሉን አስቀጥለዋል ህወሃትም ሌሎች የጸረ ጭቆና ሃይሎችን በማስተባበር ትልቅ ኢትዮጵያዊ ማእበል እንዲፈጠር ደርግን የመሰለ ትልቅ የተደረጀ ሃይል ያለው መንግስት እንዲደመሰስ አድርጏል.. ይህን ሲያደርግ ደግሞ ግብታዊ በሆነ ሁኔታ ሳይሆን ረጂም እቅድ ነድፎ ከድል በሁዋላ ሊኖር ስለሚችለው ልማት .. ሊኖር ስለሚገባው ሰላም ትበተናለች የተባለችውን ሃገር ደሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ እንደት የሃገሪቱ ብሀር ብህረሰቦች እና ህዝቦች እኩል የሉአላዊ የስልጣን ባለቤት እንዲሆኑ እኩል በተመጣጣኝ ውክልና የስልጣን ባለቤት እንዲሆኑ የሚያስችል ሃሳብ በማመንጨትና በማሳተፍ አደራጅⶆል አታግⶀል ስለዚህ ትምክተኞች የሚጠሉት ለዘላለም እንዳይመለሱ አድርጎ ከስራቸው እንዲመነገሉና ሃሳባቸው የጥፋት እንደሆነ የሃገራችን ህዝቦች እንዲያውቁ ስላደረገ በዚህም ዙሪያ የነሱ ጥፋት ላይ ያታገለ ድርጅት ስለሆነ ይጠሉታል የትግራይም ህዝብ የዚህ ድርጅት ምንጭ ስለሆነ ይጠሉታል ጠባቦች ለዘመናት በህዝቦች ስም እየነገዱ በተጨባጭ ግን ለህዝቡ ሰላም ልማት ዲሞክራሲ እኩልነት አብዮታዊ ሃይሎች ከነዚህ ከተበደሉት ህዝቦች ሃሳቡን በማመንጨት እና እኩል በማታገል እነዚህ ሃይሎች ገዥ ሆነው እንዳይቀመጡ ያደረገ ስለሆነ ይጠሉታል ለህዝቡ ታድያ የበላይነት ያለ ለማስመሰል ፣ምንድነው ተስሎ የሚቀርበው የሚለውን በሁለተኛ ደረጃ ማየት ያስፈልጋል ዛሬም ቢሆን የትግራይ ህዝብ ትናንት ታግዬ አታግዬ ለወገኖቼም ድጋፍ ሰጥቼ ለውጥ በማምጣቴ የተለየ ጥቅም ይገባኛል አላለም እንደማንኛውም የኢትዮጵያ ህዝብ ይልቁንም ተራሮችን እና ድንጋይ ዛሬም ትልቅ የተፈትሮ ሃብት ስራ እየሰራ ውሃ እያመነጨ ከድህነት ጋር አዲስ ትግል የገጠመ ህይወቱን በዚህ መሰረት ላይ ጥሎ እየሰራ ያለ ህዝብ ነው ህወሃት እንደ ድርጅትም በዚሁ መንገድ በሚያስተዳድርበት ክልል የህዝቡን አቅም አስተባብሮ ልማት እንዲመጣ ሰላም እንዲሰፍን ዲሞክራሲያዊ መብት እንዲረጋገጥ ለኢትዮጵያም ህዝቦች ከድህነት እና ከጉስቁልና እንዲወጡ ለማድረግ አመራር በመስጠት ላይ ያለ ድርጅት ነው በሃገር አቀፍ ደረጃም በሚሰጠው አመራር የጋራ ድርሻውን በተዋጽኦው ልክ እያበረከተ የሃገራችን ህዝቦ እነዚህን ቅድም ያልኩዋቸውን የሰላም የልማት የዲሞክራሲያዊ አስተዋጽ ኦዎች እንዲያድጉ እያደረገ ያለ ድርጅት ነው ይህ መሆኑ ሳይጠፋቸው ይህን እውነት ሳያጡት ጥቂት በህወሃትና በትግራይ ህዝብ ስም የሚነግዱ ሰዎች የትኛውም ብሄር ውስጥ እንዳሉ ጥገኞች ትግራይ ውስጥም አሉ........... የትኛውም ብሄር ውስጥ እንዳለ አመራር ብልሽት ህወሃትም ውስጥም አለ ... ይህን የአመራር ብቻ ነቅሶ በማውጣት የትግራይ የበላይነት ያለ በማስመሰል ቅድም ባልኰዋቸው ሁኔታዎች መንግስት ማቅረብ በነበረብን የልማት በ አግባቡ ያልተጠቀሙ የህብረተሰብ ክፍሎችን ልብ በሚኮረኩር መንገድ ሌሎች ህዝቦች መልማት ያልቻሉትና በአግባቡ ያልተጠቀሙት ድርሻቸውን ህወሃት ሰለወሰደው ነው ድርሻችሁን የትግራይ ህዝብ ወስዶት ነው ብሎ ወደተሳሳተ ታርጌት እንዲተኩስ .....ትክክለኛ በሽታ መጀመሪያ የራስን አመራር ማጥራት ቀጥሎ በራስ አቅም ያሉ ልማት ማልማት ለሁሉ ፍትሃዊ ልማት ማምጣት ..... በትግራይ ህዝብ ስም እና በ ህወሃት ውስጥ ያለ ብልሽትም ካለ ደህዴን ውስጥ እንዳለ ኦህዲድ ውስጥ እንዳለ ብአዴን ውስጥ እንዳለ እንዳይታገሉ ወደዚህ ቦታ ወሰተሳሳተ ታርገጥ እንዲተኩሱ በማድረግ የሚሰሩበት ምክንያት ሃይል ለማሰባሰብ አስበው ነው እና ዋናው ከስር ከመሰረታቸው እንዲነቀሉ ስላደረገ የመነሻ ትግሉ ጠንሳሽ እሱ ስለሆነ እሱን ከመታህ ተመልሰህ ያንን ያጣሀውን ቦታ ለመያዝ ትችላለህ ከሚል የተሳሳተ ግምት ነው ስለዚህ ይህ መጀመሪያውኑም ቢሆን ይህ ለውጥ እና ትግል በምኞትና ዝም ብሎ በቀላል መስዋትነት የመጣ አይደለም ከፍተኛ ዋጋ የተከፈለበት ከፍተኛ ትግል የተደረገበት የህዝቦች መስዋእትነት የተከፈለበት ትግል ነው ስለዚህ አሁንም መጀመሪያ ወደ ውስጥ ማየት .. እንደ ኢህአዴግ እንደ ድርጅት ያሉበትን ችግሮች ማጽዳት ..እራሱ ከነዚህ ችግሮች መጀመሪያ ነጻ ከሆነ በሁዋላ የዚህ ችግር አስተሳሰብ ለመስረጽ የሞከሩባቸው ቦታዎችን የነሱ ነጻ መሬትና ነጻ ወረዳ እንዳይደለ እንዲገነዘቡ ማድረግና ወደልባችን ተመልሰን በመንግስት እና በድርጅት ውስጥ ያለ ብልሽት እና የመልካም አስተዳደር ችግርን በማረም የህዝቦች ተቃሚነትን በማረጋገጥ የወጣቱን ተጠቃሚነት በፍጥነት ምላሽ በመስጠት ወጣቱም በሃገር ግንባተ ውስጥ የራሱን አስተዋጽ እንዲያደርግ በማስቻል እነዚህን ከንቱ ተስፈኞች ተስፋቸው ከንቱ እንደሆነ ማሳወቅ ይገባል »
በጋዜጠኛ ተክለሃይማኖት ገብረመድህን 
መቀሌ 

2017 ጁን 17, ቅዳሜ

ኢትዮጲያን መልሶ የቀይ ባሕር ሀይል የሚያደርግ ፖሊሲ ያስፈልጋል ~ ጻድቃን ገብረትንሳኤ

ኢትዮጲያን መልሶ የቀይ ባሕር ሀይል የሚያደርግ ፖሊሲ ያስፈልጋል ~ ጻድቃን ገብረትንሳኤ [+Audio]

በስራ ላይ ያለው የብሔራዊ ደህንነትና የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ በቀይ ባህር ላይ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች ለኢትዮጲያ ያላቸውን አንድምታ ታሳቢ ያላደረገ እና ችግር ያለበት ነው በማለት ሌተናንት ጄኔራል ጻድቃን ገብረትንሣኤ ተቹ።
የቀድሞው የሀገር መከላከያ ኤታማጆር ሹም ጻድቃን ገብረትንሣኤ ይህን የተናገሩት ከመንግስታዊው አዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር በቅርቡ ባደረጉት ቃለ-ምልልስ ነው። ጋዜጣው የጻድቃንን አስተያየቶች በከፊል ያላቀረባቸው ቢሆንም፤ ሆርን አፌይርስ ሙሉ የድምጽ ቅጂው ደርሶታል።
ጄኔራል ጻድቃን ‹‹ኢትዮጲያ ትልቅ ሀገር ነው። በቀይ ባህር የሚደረገው ሁሉ ያሳስበናል። እኛ የቀይ ባህር ሀገር ነን። ከቀይባህር የተነጠልን እንድንሆን መፍቀድ የለብንም።….በኤርትራ ሳቢነት  ሆነ  በራሳቸው በቀይ ባህር አካባቢ የሚንቀሳቀሱ የተለያዩ ሀይሎች አሉ። ቀይ ባህር  እኛን እና  የባህረ ሰላጤው ሀገራትን የሚለይ ባህር ነው። ከፍተኛ የንግድ እንቅስቃሴ የሚደረግበት ነው። የኛ የብሔራዊ ደህንነትና የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ በዚህ ረገድ ውጤታማ ነው ብዬ አላስብም። እንደገና መታየት ያለበት ትልቅ ነገር አለ›› ሲሉ አሳስበዋል፡፡
ኢትዮጲያን መልሶ የቀይ ባህር ሀይል ማድረግ የፖሊሲው ግብ ሊሆን እንደሚገባ የጠቆሙት ጻድቃን፤ ‹‹ይህ ማለት የግድ ወሮ በመያዝ ላይሆን ይችላል….ካለን የሕዝብ ብዛት፣ ለባህሩ ካለን ቅርበት፣ ከኢኮኖሚያችን እድገት አንጻር፤  ሌሎች ለዝንተ-ዓለም ቀይ ባህር የማንጠጋበት ሁኔታ እየፈጠሩ ባሉበት ሁኔታ ዝም ብለን ማየት የለብንም›› ብለዋል።
‹‹ይሄ ለአሁኑ ብቻ ሳይሆን ለወደፊቱም ለመንቀል አስቸጋሪ የሆነ  ነቀርሳ እየተተከለ ያለ ነው የሚመስለኝ›› በማለት፤ ከዚህ አንጻር ነባሩ ፖሊሲ ‹‹ትልቅ ችግር ያለበት ነው›› በማለት አጽንኦት ሰጥተዋል።

ጠ/ሚ ኃይለማርያም ደሳለኝ ስለ ባቡር ኔትወርክ በዓድዋ ያደረጉት ንግግር

ጠ/ሚ ኃይለማርያም ደሳለኝ ስለ ባቡር ኔትወርክ በዓድዋ ያደረጉት ንግግር[+audio]

እኔ እርግጠኛ ነኝ ….. ምናልባት በኛ እድሜ ላይደርስ የሚችል ነገር ካልሆነ በስተቀር ….. ኢትዮጲያ የእድገት ጉዞ ጀምራለች፤ ያ የእድገት ጉዞ የጊዜ ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር ባቡር ጊዜውን ጠብቆ እዚህ ዓደዋ ላይ እንደሚደርስ ጥያቄ የለውም፡፡ አሁን ጥያቄው ምን አቅም አለን እንዴት አድርገን እናደርሳለን ፍላጎት ብቻውን ውጤት ስለማይሆን፡፡ ፍላጎት ጥሩ ነው፤ ራዕይ ማስቀመጥ ጥሩ ነው፡፡ ራዕይ አለን ነገር ግን ደግሞ አቅምም ነው፡፡
ባቡር እንደምታውቁት በእያንዳንዷ ኪሎሜትር በፈረንጆቹ ሜዳ ከሆነ 4 ሚልየን ዶላር በኪሎሜትር ተራራ ከሆነ እንደዚህ ወደ ሰሜን አካባቢ – በእርግጥ ደቡብ ብዙ ተራራ አለ ሰሜንም ምስራቅም አለ ግን – ተራራማ በሚሆንበት ግዜ ተራሮች ስለሚቆፈሩ በዚያ ውስጥ ስለሚታለፍ – ያው ባቡር እንደምታውቁት እንደ መኪና ዳገት አይወጣም ቀጥ ብሎ ሰንጥቆ ነው የሚሄደው ስለዚህ በጥሰን ነው መሄድ የምንችለው – ያ ደግሞ በኪሎሜትር ከ7-8 ሚልየን ዶላር ነው፡፡ ያ ማለት 7 ግዜ 20 ከ140-160 ሚልየን ብር ነው በኪሎሜትር፡፡ አስቡ እዚች ከተማ ውስጥ አንዷ ኪሎሜትር ምን ማለት እንደሆነች ታውቃላችሁ፡፡ እዛች ላይ ከ140-160 ሚልየን የሚሆን ብር ማውጣት አለብን ማለት ነው፡፡ ይሀ ለመንገዱ ብቻ ነው በላዩ ላይ የሚሽከረከረው ደግሞ ሌላ ወጪ ነው፡፡
ስለዚህ ይሄ ነገር ያው አቅማችን እየጎለበተ ሲሄድ…አቅም ማለት የእናንት አቅም ነው፤ የመንግስት አቅም ማለት የህዝብ አቅም ነው፡፡ የህዝቡ አቅም ደረጃ በደረጃ እያደገ ሲመጣ…እኛም እኔ አሁን ዓደዋን የዛሬ ሶስት አራት አመት በፊት ስድስት አመት በፊት መጥተን ነበር፡፡ አሁን ያለችው ዓደዋ እና የዛሬ ስድስት አመት የነበረችው ዓደዋ ሰማይና ምድር ነው፡፡ ስለዚህ እናንተ አደጋችሁ ማለት ባቡሩ ሊመጣ እየተቃረበ ነው ማለት ነው፡፡ከህዝብ እድገት ጋር አብሮ የሚሄድ ነው ማለት ነው የመንግስት አቅም የህዝብ አቅም ስለሆነ፡፡
ከዚህ አኳያ ሳየው መምጣቱ አይቀርም ግን ደረጃ በደረጃ…መጀመሪያ ዋናውን የኢትዮጲያ ከተማ አዲስ አበባ ከወደብ ጋር ማገናኘት… ምክንያቱም ሁላችንም ጉሮሯችን የሚታነቀው ወደቡ ሲታነቅ ነው፡፡ ስለዚህ መጀመሪያ ወደቡን ከፍተን ጉሮሯችን ክፍት ማድረግ በሂደት ደግሞ ፖርት ሱዳን እንዳላችሁት ወደብ መጠቀም ጀምረናል አሁን በትንሽ በትንሹ እያሳደግነው እንሄዳለን፡፡ የዛን ግዜ ወደ ሰሜኑ ሰሜን ምዕራብ የኢትዮጲያ ክፍል እንደዚሁ እየዘረጋን መሄዳችን አይቀርም ከሱዳን ጋርም ተስማምተን፤ አብዛኛውበሱዳን መስመር ላይ ነው የሚሰራው እንግዲህ የሱዳኖችንም አቅም ይጠይቃል ማለት ነው፤ የእኛ አቅም ብቻ የትም አያደርሰንም ሱዳኖችም በዛው መጠን አቅማቸው እያደገ ሲሄድ በጋራ ሆነን የምንሰራው ስራ ይሆናል፡፡
መምጣቱ አይቀርም ግን እኔ ደግሞ ያልሆነ ቃል ልገባላችሁ አልችልም አይገባኝምም፡፡ አቅም በጣም ይፈታተናል ባቡር፡፡ በጣም አቅም ሰለሚፈታተን የተወሰነ ግዜ መውሰዱ አይቀርም፡፡ ስለዚህ እኛም እየለማን በትእግስትም እየጠበቅን እየሰራን ስንሄድ ባቡር ሊመጣ ይችላል ብዬ አምናለሁ፡፡ ምናልባት ደግሞ ሰላም ከፈጠርን የሚቀርብ ነገር እንዳለ ታውቃላችሁ፡፡ እና የዛን ግዜ ሊፈጥን ይችላል፡፡ ለማንኛውም ይሄ ነገር ሊመጣ የሚችል እንደሆነ ሰንቀን መቸም ራዕይ ትልቅ ነገር ነው ራዕይ ሰንቀን መታገል ያለብን ይሆናል ማለት ነው፡፡

የኢህአዴግ አመራር “የበላይነት” የሚባል የለም

የኢህአዴግ አመራር “የበላይነት” የሚባል የለም ብሎ ደምድሟል - ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል [+Video]

ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል የትግራይ የበላይነት የሚባለው ስሞታ <<ምክንያቱ ፖለቲካዊ [ስለሆነ] ምላሹም ፖለቲካዊ ነው፡፡ ላልገባው በማብራራትሆን ብሎ የሚለውን ደግሞ በመግጠም መስተካከል ያለበት ነው፡፡… እንደ ኢህአዴግ “የበላይነት” የሚባል ነገር የለም ተብሎ ተደምድሟል፣ አለ ብሎ ሲያነሳ የነበረም ሳይቀር ማለት ነው፡፡ አንዳንዱ ሆን ብሎ ፖለቲካዊ አጀንዳ ስላለው አንዳንዱ የራሱን ድከመት ለመሸፈን አሻግሮ Divert ለማድረግ (externalization) ተብሎ የመጣ ጉዳይ ነው በሚል በግልፅ ነው የተደመደመው>> ብለዋል።
የኢንፎርሜሽን ኮሚኒኬሽን ቴክኖሎጂ ልማት ሚኒስትር እና የህወሓት ም/ሊቀመንበር ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል ይህን አስተያየት የሰጡት ባለፈው ቅዳሜ በተለይ ከሆርን አፌርስ ጋር ባደረጉት ቆይታ ነው፡፡ ኢንተርኔት ተዘግቶ የነበረ በመሆኑ ቃለ-ምልልሱን ያትምነው ትላንት እና ዛሬ ነው።
ትላንት በሆርን እፌይርስ እንግሊዝኛ እና በሆርን እፌይርስ YouTube አካውንት ላይ ባወጣነው የቃለ-መጠይቁ ክፍል አንድ ላይ፤ የቴሌኮም አገልግሎት በመንግስት ሞኖፖል ስር  መሆን፣ የኢንተርኔት  መዘጋት፣ የገጠር ቴሌኮም ሽፋን እንዲሁም በመንግስት ስራ ላይ ሆነው ዶክትሬት ትምህርታቸውን ስለማጠናቀቃቸው ከሆርን አፌይርስ ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
በጥልቅ ተሃድሶ  ውይይቶች ላይ ስለቀረበው የትግራይ የበላይነት አጀንዳ ላቀረብነው ጥያቄ ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል የሰጡትን ማብራርያ እና ስለሶሻል ሚድያ የሰጡትን አስተያየት ደግሞ ዛሬ በሆርን እፌይርስ YouTube አካውንት ላይ ባወጣነው የቃለ-መጠይቁ ክፍል ሁለት ላይ ተካትቷል።
ከዚያ መካከል፤ በጥልቅ ተሃድሶና ‹‹የትግራይ በላይነት›› ስሞታ ጋር በተያያዘ የሰጡትን መልሶች ጭማቂ በጽሑፍ እንደሚከተለው አቅርበነዋል፡፡
(ይህ ጭማቂ እንጂ እንደወረደ የተፃፈ አይደለም)
ሆርን አፌይርስ፡- ባለፈው ነሐሴ በሰጡት ፕሬስ ኮንፍረንስ ላይ “የብሔር የበላይነት” ስለሚባለው ስሞታ ሲያብራሩ፤  ስሞታው አንዳንዴ ከፈጠራ አሉባልታ አንዳንዴ ደግሞ ከperception የሚመነጭ መሆኑን ገልጸው ነበር። ያንን ለማረቅ የሚሰሩ ስራዎች እንደሚኖሩም ጠቁመው ነበር። አሁን በምልሰት ስናየው “የትግራይ የበላይነት” የሚለውን ስሞታ ለማረቅ የተያዘው ስትራቴጂ የትግራይ የልማት ፕሮጀክቶችን ማጠፍ ነው ወይ የሚል ጥርጣሬ ፈጥሯል። ለምሳሌ የወልቃይት ስኳር ፋብሪካ፣ የመቐለ-ሽረ ባቡር መስመር፣ የወልዲያ-መቐለ ባቡር መስመር፣ በኢፈርት ታቅደው የነበሩ የኬሚካልና የብረታብረት ፕሮጀክቶች የባንክ ብድር ማጣት፣ ወዘተ። አንድ በአንድ እየዘረዘሩ መልስ ላይሰጡባቸው ይችላሉ። ዋናው ነጥብ ግን የትግራይ የበላይነት የሚለውን ስሞታ ለማስታመም ሲባል የትግራይን ፕሮጀክቶች ማጠፍ እንደአቅጣጫ ተይዟል ወይ?
ዶ/ደብረፅዮን ገብረሚካኤል፡- ወደዚያ ከመሄደህ በፊት “የትግራይ የበላይነት” የሚለው “ለምን?” የሚለው ነው መመለስ ያለበት፡፡ ምክንያቱን አውቀህ ነው ለዚያ መፍትሄ የምትሰጠው፡፡ ለጨጓራ በሽታ የኩላሊት መድሀኒት ሌላ በሽታ ያመጣል እንጂ ሊፈታ አይችልም፡፡ ትክክለኛውን ምንጩ ለይትህ በምንጩ ትሰራለህ ማለት ነው፡፡ ስለዚህ “የበላይነት“ የሚባለው ከፕሮጀክቶች ጋር የተያያዘ ነው ወይ? ከሚገባው በላይ የተሰራ ስራ አለ ወይ ነው? ምክንያቱ እሱ ከሆነ ከሚገባው በላይ ፕሮጀክት በመንግስት የተሰራ ስራ ካለ “አዎ ይሄ ተገቢ አይደለም“ ብለህ ታስተካክለዋለህ ወደ መቀነስ ትሄዳለህ፡፡ ምንጩ እሱ ካለሆነ እሱ አይደለም መፍትሄ ማለት ነው፡፡ ወደ ፕሮጀክት አትሄድም፡፡ ወደ ዋናው ምንጩ ነው የምትሄደው፡፡
/የትግራይ የበላይነት/ የሚባለው አንዳንዱ ፐርሰፕሽን /የተዛባ አመለካከት/ ነው አንዳንዱ ደግሞ ፈጠራ ነው፤ የሌለን ነገር እንዳለ አድርጎ የማቅረብ ፈጠራ ነው፡፡ ለምን? ለሚለው ምክንያት አለው፡፡ /በኢህአዴግ/ አንዱ በደንብ የገምገምነው እሱን ነው ፤“የትግራይ የበላይነት“ የሚባል የለም ነው፡፡ የለም፡፡ ለምን? ሄደን ሄደን ስርእቱን እንየው ነው፡፡ ስርአቱ “የበላይነት“ እንዲኖር ይፈቅዳል ወይ? የምንፈቅድ አለን ወይ? የትግራይ ብቻ ሳይሆን የሌሎችም፡፡ ይሄ ስርአት ካልፈረሰ በስተቀር ሊኖር አይችልም፡፡ ይሄ ስርአት የትግራይንም የሌላንም የበላይነት አያስተናግድም፡፡
ከፌዴራል ጀምረህ የስርአቱን አወቃቀር ነው የምታየው፡፡ የበላይነት ዝም ብሎ ሊመጣ አይችልም እኮ ዝም ብሎ ሀሳብ ሊሆን አይችልም ፤ አወቃቀሩ የሚፈቅድ ከሆነ ነው ፣ ካልሆነ ያው ስሜት ብቻ ሆኖ ይቀራል፡፡ /አወቃቀሩ ካልፈቀደ/ “የበላይነት“ የሚፈልግም ካለ ስሜት ብቻ ፤ “የበላይነት አለ“ የሚልም የራሱ ግምት ብቻ ሆኖ ይቀራል፡፡ በተግባር ይህን የሚፈቅድ ስርአት የለንም፡፡ በህዝብ ተወካዮችም በፌዴሬሽን ምክር ቤትም ሆነ በሚኒስትሮች ምክር ቤት በህዝብ ብዛት መጠን ነው የተወከለው፡፡ እንደ ብሄር እኩል ነን፡፡ ውክልና ግን በህዝብ ብዛት ነው የተኬደው፡፡ ስለዚህ አንዱን የበለጠ የሚጠቅም ነገር ይዘህ በድምፅ ሊያልፍ አይችልም ማለት ነው፡፡ በፖለቲካ ሃላፊነትም እኩልነት ነው የሚታየው፡፡ በኢህአዴግ ምክር ቤትም ሆነ ስራ አስፈፃሚ ሁሉም የፖለቲካ ድርጅቶች እኩል ነው ውክልና ያላቸው፡፡ ለምሳሌ አንጋፋው ህወሓት ነው በሚል የተለየ ተጨማሪ ቁጥር አይሰጠውም፡፡ ብዙ ውሳኔ በሚወሰንበት የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ከ36ቱ ከሁላችንም እኩል ዘጠኝ ነው የተወከለው፡፡ አብዛኛው ያልተስማማበት ስለማያልፍ ማንም ድርጅት ዘጠኝ ሰው ይዞ የበላይነት ሊያመጣ አይችልም፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንኳን የፈለገውን ሁሉ ሊወስን አይችልም፡፡ /በህግ/ የተሰጠው ሃላፊነት አለ የተወሰነውን በራሱ ያስፈፅማል ሌላው ወይ በፓርቲ ወይ ከላይ ሆኖ በሚመራው መንግስት (ካቢኔ) የሚታይ ነው የሚሆነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር በመሆኑ ወይም የድርጅት ሊቀመንበር በመሆን እንዲወሰን ተፅዕኖ ማሳደር ይችላል ውሳኔ ግን ሄዶ ሄዶ የጋራ ነው፡፡ ለምሳሌ በካቢኔ አሁን 30 ነን፡፡ ድሮም ዛሬም ህወሓት ሶስት ሚኒስትር ብቻ እኮ ነው ያለው፤ ሶስት ይዘህ ደግሞ እንዴት ነው የተለየ ልታስወስን የምትችለው?  ስለዚህ “የትግራይ የበላይነት“ ይቅርና አሁን መለስ እያለም አለ ሊባል አይችልም፡፡ ከህወሓት የመጣ ነው በሚል ብቻ “የበላይነት“ ልትል አትችልም፤ አብዛኛው ካልተቀበለው ጠቅላይ ሚኒስትር ስለሆነ ብቻ ሊወስን አይችልም፣ ይሄ ደግሞ ይታወቃል ታሪኮች አሉ፡፡
አንድ ሚኒስትርም ብቻውን ሊወስን አይችልም፡፡ ለምሳሌ እዚህ ቴሌኮም ስለምመራ ለብቻዬ ልወስን አልችልም፣ በጋራ ወስነን ነው ወደ ስራ የምንሄደው፡፡ ቴሌኮሙም መብራቱም ሌላውም ተደራሽነት በእኩልነት የህዝብ ብዛቱ የክልሉ ስፋት ወዘተ እየታየ በቀመር ነው፡፡ የገጠር ቴሌኮም ካልክ በሀገሪቱ ሁሉ ያለ ቀበሌ ወረዳ ማለት ነው፡፡ የትራንስፎርሜሽን እቅዱን ፓርላማ ነው ያወጣው፡፡ ወደ ክልሎችም ስትሄድ ሁሉም ድርጅት የራሱን ነው የሚያስተዳድረው፡፡ ህወሓት ኦሮሚያን ወይም አማራ ክልልን ሊያስተዳድር አይችልም፡፡ ስርአቱ አይፈቅድም፡፡ ስለዚህ በክልል የበላይነት የሚባለው የሌለ አምጥቶ የመለጠፍ ፈጠራ ነው፡፡ ስርእቱ በዚህ መሰረት አልተገነባም አይሰራም፡፡
ሌላው መሰረተ ልማት ነው፡፡ ፕሮጀክትም ከበጀት ነው፡፡ በጀት በቀመር ነው የሚሰራው፣ በህዝብ ብዛት ያለው አብላጫውን ይወስዳል፡፡ በዚያ መሰረት ትግራይ 5ኛ ላይ የምትገኘው፡፡ ክልሉ ያንን በብዛቱ መጠን ያገኛትን ይዞ ነው ስራ የሚሰራው፡፡ ፌዴራል የሚሰራቸው ፕሮጀክቶች ላይ ደግሞ የፌዴራል መንግስቱ በሁሉም ክልሎች አመጣጥኖ ነው የሚሰራው፡፡ ሄዶ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሚወሰነው፡፡ ለትግራይ የተለየ ነገር ይዞ ተኪዶ በየት በኩል ነው የሚፀድቀው? ሌላው ምን ይሰራል? የራሱን ጥቅም አሳልፎ አንዱ ብሄር ይጠቀም ብሎ የሚወስን ሰው ሊኖር አይችልም፡፡ እንደዚህ አይነት ጭፍን ህዝብ አይደለም፡፡ ሁሉም የየራሱን ፍላጎት ግን በእኩልነት እንዲሟላለት የሚፈልግ ነው፡፡ መቼም መሰረተ ልማት ደግሞ ሰርቀህ ልትሰራው አትችልም፡፡
ሆርን አፌይርስ፡- ግን እኮ አሁን ያለው ጥርጣሬ ምንድነው “የትግራይ የበላይነት እያሉ ሲያሳቅቋችሁ ከጭቅጭቁ በማለት፣ በይሉኝታ በመያዝ አንዳንድ ነገሮችን፣ fair የሆነውን ነገር ራሱ፣ እየተዋችሁ ነው” የሚል ነው።
ዶ/ደብረፅዮን ገብረሚካኤል፡-  ገባኝ።፡ግን መነሻው እሱ ስላልሆነ ነው እኮ ያልኩህ፣ በዚያም እኛ ወደ ኋላ የምንልበት ምክንያት የለም፡፡ ምክንያቱ እሱ ስላልሆነ ያልኩህ ለዛ ነው፡፡ ስርአቱ አይፈቅድም፣ ስለዚህ ለምን ወደ ኋላ ትላለህ፡፡ የበላይነት የሚባል የለም ነው እያልን ያለነው፡፡ ፕሮጀክት ተጨማሪ ብትወስድ ኖሮ ትክክል ነው፣ ግን የለም፣ በየት አድርገህ፡፡ ስለዚህ ወደኋላ ልትል አትችልም፡፡ ማካካሻ ሊሆን አይችልም ይሄኛው፡፡
“የትግራይ የበላይነት አለ” የሚባለው መሰረቱ ሌላ ነው፡፡ ፖለቲካዊ ነው፡፡ አንዱ ምክንያት ወደ ኋላ ታሪክ ተኪዶ ያለፈውን ስርአት በማፍረስ ላይ ህወሓት የተለየ ሚና ነበረው ከሚል ነው፡፡ ሁሉም የየራሱን ሚና የተጫወተ ቢሆንም ህወሓት በሂደቱም በመስዋእትነቱም ጎላ ያለ ሚና እንደነበረው ይታወቃል፡፡ ስለዚህ ከዚያ ተነስቶ ቅሬታ ያለው ወገን አለ፡፡ የቆየ ቅሬታ ማለት ነው፡፡ እነዚህ ተደጋግመው የሚነሱት የመከላከያ የደህንነት ተቋማትም የሆኑትም ታሪኩ ከኋላ የተነሳ ነው፣ ከትግል የመጣና የገባ ሀይል አለ እዚያ፡፡ ያ እስካለ ድረስ ህዝብ እስካገለገለና ውጤታማ እስከሆነ ድረስ ሁሉንም ያገለግላል የአንድ ወገን ስራ አይደለም የሚሰራው፣ በሂደት ለማመጣጠንም የሚሰሩ ስራዎች አሉ፡፡ በሚመስሉ ነገሮች ላይ (በፐርሰፕሽን ችግር) ተመስርቶ የሚነሱትንም የስርአቱን አወቃቀርና አሰራር በማስረዳት ነው የሚፈታው፡፡
ሌላው ምክንያት ስርአቱን ለመቃወምና ለማፈረስ የሚፈልግ የፖለቲካ አጀንዳው ስለሚያደርገው ነው፡፡ በፊት (ትግራይ) ያልተሰራ ተሰራ እየተባለ አልነበረ እንዴ የሚወራው? የሚመስል ነገር ስታመጣ ደግሞ ስርአቱን ለማፈረስ ህዝቡን የበለጠ ለማንቀሳቀስ ስለሚመች ትጠቀምበታለህ ፤ ከወደቀ ደግሞ ሌላ አጀንዳ ትፈልጋለህ ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ምክንያቱ ፖለቲካዊና ስርአቱን ለማፍረስ ለመጠቀም ወደ ዘር ቅስቀሳ የሄደ ነው ማለት ነው፡፡
ስለዚህ ምክንያቱ ፖለቲካዊ ከሆነ ምላሹም ፖለቲካዊ ነው፡፡ ላልገባው በማብራራት ሆን ብሎ የሚለውን ደግሞ በመግጠም መስተካከል ያለበት ነው፡፡ የሚነሱት በፕሮጀክት ላይ የሚነሱ አይደሉም፣ ወደ ፕሮጀክት አይሄድም፡፡
ሌሎቹ (ሳይሰሩ የዘገዩት) ፕሮጀክቶች ጉዳይ ከዚህ ጋር ምንም ግንኙነት የላቸውም፣ የየራሳቸው ምክንያቶች አላቸው፡፡ የባቡሩ ጉዳይም ተደጋግሞ ሲነሳ ሰምቸዋለሁ፡፡ አይሰራም አይደለም፡፡ ይሄ ከመቐለ ወደ ሽረ የሚሄደው በሁለተኛው የትራንስፎርሜሽን እቅድ ላይ ሊታይ ይችላል – ጥናት (ይደረግበታል) ብለን ነው የያዝነው፣ አሁንም ጥናት ነው፡፡ ስለመስራት አሁን ልናወራም እኮ አንችልም፡፡ እቅድ የያዝነው ለጥናት ነው፣ ክጥናት በኋላ ነው መስራት የሚመጣው፡፡ ስለዚህ አልተቀየረም፡፡ የተቀየረ ነገርም አሁን የለም፡፡ ገንዘቡ “ውድ ነው” “አነስተኛ ነው”… በኋላ ነው የሚታየው ማለት ነው፡፡ ስለዚህ በዚህ ወደ ኋላ የተመለሰም ነገር የለም አሁንም ይቀጥላል፡፡
የወልድያ-መቐለውም ሌላውም በብድር ነው የምንሰራው፡፡ ሌሎችም ፕሮጀክቶችም አሉ የምንፈልገውን ብድር ያላገኘንባቸው፣ ትግራይ በመሆኑ አይደለም፡፡ ከትግራይ ምንም የማያገናኛቸው የኢነርጂ ፕሮጀከቶችም ላይ ብድር ያላገኘንባቸው አሉ፡፡ ስለዚህ ጥረት ነው ማድረግ አለብን ማለት ነው፣ በእቅድ አስቀምጠነዋል፣ እኛም ለመስራት ነው ጥረት እያደረግን ያለነው፡፡ አክችዋሊ የወልድያውም እየተሰራ ነው፣ በመንግስት ገንዘብም ቢሆን፣ የቆመ ነገር የለም፡፡ ግን የፈለግነውን ገንዘብ አላገኘንም ተጨማሪ ጥረት እየተደረገ ነው፡፡ ስለዚህ ይሄ ሀሳብ የመቀየር ነገር ሳይሆን ብድር የማግኘት ጉዳይ ነው፣ የውጭ ምንዛሬ እጥረት እንዳለብን ይታወቃል እኮ፡፡ ስለዚህ አገር አቀፍ ችግር ነው እንጂ የታጠፈ ነገር የለም፡፡ /ለበላይነት ክስ/ ማስታገሻ የሚባል ነገርም እንደሌለ ብንገነዘብ..
ሆርን አፌይርስ፡- በዓመቱ የመጀመሪያ አጋማሽ በየመስሪያ ቤቱ በተደረጉ የጥልቅ ተሀድሶ ውይይቶች ላይ “የትግራይ የበላይነት አለ ወይ” የሚል አጀንዳ ነበር። በአጀንዳው ላይ በቂ በመረጃና ትንታኔ የተጠናቀረ ሰነድ ባልቀረበበት ሁኔታ  የተደረገ ውይይት ነው። ስለሆነምየውይይቱ ውጤት ለስሞታው legitmacy መስጠት ነው የሚል ግምገማ  አለኝ። ለምሳሌ የዚህ መሰረተ-ቢስ አስተሳሰብ ተግባራዊ መገለጫው ባለፈው ክረምት በትግራዮች ላይ የተፈጸሙትን በማሳያነት ሊቀርብና በዚያውም የሚወገዝበት ሊሆን ይችል ነበር። በተቃራኒው በቀጣይ ወራት ያየነው፤ የትግራይ ተወላጆች  “ባለፈው ክረምት ከኢሕአዴግ እህት ፓርቲዎች አንዱን ተቻችሁ” በሚል ማሸማቀቅ ነበር። በአጠቃላይ ሂደቱ ለጽንፈኞች መንግስታዊ ሽፋን የመስጠት ውጤት ነበረው የሚል ግምገማ አለ። በዚህ ላይ ምን ይላሉ?
ዶ/ደብረፅዮን ገብረሚካኤል፡- የጥልቅ ተሀድሶ ውይይቶች ሁሉም “የበላይነት አለ” እንዲል ተፈልጎ የመጣ አይደለም፡፡ በድርጅቶችም በመንግስትም አጠቃላይ ችግር አለ፣ ህዝብ የሚፈልገውን አገልግሎት እያገኘ አይደለም…ብዙ ቅሬታ አለ፣ የዚህ ቅሬታ ምንጭ በድርጅቱ ውስጥ ያለ አመራር ነው ራሱን ይፈትሽ በሚል ነው፡፡ በጥልቀት የተባለውም ለዚያ ነው እንጂ “የበላይነት” አይደለም ዋናው አጀንዳው፡፡ ግን ይፈተሽ ሲባል ቅድም ፖለቲካዊ ስራ ነው እንዳልኩት በሌለ ብዙ ይነሳ ነበርና ውይይት ያስፈልገዋል ማለት ነው፡፡ እንደዚህ ነው ይሄ ስርአት በሚል ለመወያየት..እንደዚያ ነው የተደረገው በየአካባቢው፡፡ ስለዚህ ውይይቱ የኪራይ ሰብሳቢነት፣ የመልካም አስተዳደር… በአጠቃላይ ጉድፎቻችንን እናራግፍ በሚል የተካሄደ ነው፡፡
በአንድ አጀንዳ ብቻ ልንመዝነው አይገባም፣ መራገፍ ከሚገባቸው አስተሳሰቦች አንዱ ስለሆነ ነው፡፡ እቺን ነጥዬ በሁሉም ደረጃ ውይይቶች እንዴት ነበሩ ብዬ ለማስቀመጥ አልችልም፤ የጎደለ ነገር እንዳለ ግን አውቃለሁ፡፡ እንደ አጠቃላይ የትምክህትና የጠባብነት አመለካከቶች ጋር በተያያዘ መራገፍ ያለባቸው አስተሳሰቦች አካል አድርገን ነው የምንወስደው፡፡ መገለጫዎቹ ብዙ ናቸው ይሄ አንዷ ናት፡፡ ስለዚህ ፍተሻው ላይ የተጓደለ አለ በዚህም ላይ ሊጎድል እንደሚችል መገመት አይከብድም፡፡ ቢሆንም ነገሮች ለውይይት መውጣቱ ሁሉም ያለውን ማውጣቱ ጥሩ ነው፡፡ አመለካከቶች የሚስተካከሉት በውይይት በመሆኑ መድረኩ መፈጠሩ በራሱ ጥሩ ነው፡፡
የመጀመሪያ መድረክ በመሆኑ የተጓደለ ነገር እንዳለ እናውቃለን ማለት ነው፡፡ “የበላይነት” የሚለው የሚደጋገምባቸው አካባቢዎችም ካሉ ይህንን ጨምሮ የተጓደሉ ነገሮች ላይ ተጨማሪ እንስራ ነው ያልነው፡፡ ዋናው ግን በአጠቃላ የተዛቡ እመለካከቶችን ማረም…ህዝብን ከማገልገል አንፃር ሁሉም ህዝብ ወገኔ ነው የሚል አተያይ…ከአተያይ ጀምሮ ብዙ የተበላሹ ነገሮች አሉና እሱ ሲስተካከል ይሄም አብሮ ይስተካከላል ብለን ነው የያዝነው፡፡ በሰቪል ሰርቫንቱ ብቻ ሳይሆን በድርጅቶቹ ውስጥም ራሱ በደንብ እንስራ ብለናል፡፡ ባለፈው ክረምት ከነበረው በጣም ተሻሽሏል፣ በቂ አይደለም ብለናል፡፡
አክችዋሊ እንደ ኢህአዴግ “የበላይነት” የሚባል ነገር የለም ተብሎ ተደምድሟል፣ አለ ብሎ ሲያነሳ የነበረም ሳይቀር ማለት ነው፡፡ ለምን? በውይይት እንፈትሸው ስለተባለ፡፡ እስቲ ይውጣ ከምን ተነስተን ነው አለ የተባለው በሚል ተነስቶ መልስ ተሰጥቶበታል፡፡ ስለዚህ እንደ ኢህአዴግ ይሄ አንዳንዱ ሆን ብሎ ፖለቲካዊ አጀንዳ ስላለው አንዳንዱ የራሱን ድከመት ለመሸፈን አሻግሮ Divert ለማድረግ (externalization) ተብሎ የመጣ ጉዳይ ነው በሚል በግልፅ ነው የተደመደመው፡፡
በከፍተኛ ደረጃ እንዲህ ቢሆንም ታች በሁሉም ቦታ እንደዛ እንዳልተደመደመ እናውቃለን፡፡ ስለዚህ ፕሮጀክት ቀነሳ ሳይሆን ቀጣይ ስራ መስራት አለብን እንጂ በፕሮጀክት የሚገለፅ ቅነሳ በምንም አይነት አይታሰብም፤ እሱ ስላልሆነ መፍትሄው ማለት ነው፡፡ ስለዚህ የሆነ ችግር ሲኖር ከዚያ ጋር የሚገናኝ አድርገንም መውሰድ የለብንም ስህተት ነው እላለሁ፡፡
********

Share this:

የአብዮት እና የዴሞክራሲ ትውልድ ግጭት

የአብዮት እና የዴሞክራሲ ትውልድ ግጭት

የቀድሞ የኢትዮጲያ አየር ኃይል አዛዥ ሜጀር ጄኔራል አበበ ተክለሃይማኖት ግንቦት ሃያን አስመልክቶ ከሪፖርተር ጋዜጣ ጋር ያደረጉትን ቃለ-ምልልስ አነበብኩት። ከቃለ-ምልልሱ ውስጥ በእሳቸው ዘመን ትውልድና በአዲሱ ትውልድ መካከል ስላለው ልዩነት የተናገሩት ነገር በጣም ትኩረት የሚስብ ነው። ከሁሉም በላይ ግን፣
“…ኢሕአዴግ ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ የእኛ ትውልድ የአማፂ ትውልድ ነው። የአማፂ ትውልድ የዴሞክራሲ ትውልድ መሆን አይችልም። …ስለዚህ የእኛ ትውልድ የዴሞክራሲ ትውልድ አይደለም። የአመፅ ትውልድ ነው።”
የሚለው አስተያየት በጣም አስገርሞኛል። ከመገረም ባለፈ በሁለቱ ትውልዶች መካከል ያለውን ልዩነት በዝርዝር እንድመለከት ምክኒያት ሆኖኛል። ወደ ዝርዝር ጉዳዩ ከማለፌ በፊት ግን፣ በቅድሚያ ለሜ/ጄ አበበ ተክለሃይማኖት ያለኝን አክብሮት መግለፅ እፈልጋለሁ።
ብዙዎች በራሳቸው ትውልድ እሳቤ ውስጥ መሸሸግ ይመርጣሉ። ወደ እውነት ከመሄድ ይልቅ፣ እውነት ወደ እነሱ እንድትመጣ ይጠብቃሉ። ነገር ግን፣ ሰው እውነትን ፍለጋ ይሄዳል እንጂ እውነት ሰውን ፈልጎ አይመጣም። ከዚህ አንፃር ሜ/ጄ አበበ ብዙ ርቀት የተጓዙ ይመስለኛል። በሁለት ትውልዶች መካከል ያለውን መሰረታዊ ልዩነት ለመረዳትና ይህንንም ለማሳወቅ ያደረጉት ጥረት የሚያስመሰግን ነው። ለሁሉም ነገር “ድሮ ቀረ…” ማለት በሚያዘወትረው ማህብረሰብ ውስጥ “ድሮ ቀረ፣ በአዲስ ተቀየረ…” የሚል ሰው መገኘቱ በራሱ ትልቅ ነገር ነው። በአጠቃላይ፣ “እኔ ብቻ ልክ ነኝ” በሚል “አክራሪ” ትውልድ ውስጥ ስህተትን ለመቀበል ዝግጁ በመሆናቸው ብቻ ለሜ/ጄ አበበ የተለየ አክብሮት አለኝ። 
ከላይ ወደ ተነሣው ሃሳብ ስንመለስ፣ ሜ/ጄ አበበ የእሳቸው ትውልድ ለዴሞክራሲ የማይመች አማፂ ትውልድ መሆኑን በግልፅ አስረድተዋል። አሁን በስልሳዎቹ አማካይ እድሜ ላይ ያለው አመፂ ትውልድ (የሜ/ጄ አበበ የእድሜ እኩያዎች) እና በአዲሱ ትውልድ መካከል ትልቅ ልዩነት ተፈጥሯል። ይህ ልዩነት ሀገሪቱን ወደ ለየለት ግጭት እየወሰዳት ይገኛል። ይህ ነገር አስቸኳይ መፍትሄ ካልተሰጠው ኢትዮጲያን ሁሉን-አቀፍ ወደ ሆነ ግጭት ውስጥ ያስገባታል። ግጭቱ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ፣ እንዲሁም ወታደራዊ ሊሆን ይችላል። ከዚህ ግጭት ነፃ የሆነ ቀጠና ወይም ገለልተኛ የሆነ አካል ሊኖር አይችልም። ምክንያቱም ይህ ግጭት የትውልድ ግጭት ነውና። አዎ…የሁለት ዘመን ሰዎች፡- የአብዮት እና የዴሞክራሲ ትውልድ ሰዎች ወደ ግጭት እያመሩ ነው። 
በየትኛውም ሀገር የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ላይ የሁለት ትውልድ አሻራ ያርፍበታል። የአብዮታዊው ትውልድ እና የዴሞክራሲያዊው ትውልድ አሻራ። በመጀመሪያ ደረጃ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የሚያስፈልገውን መሰረት የሚያቆመው የአብዮቱ ትውልድ ነው። በመቀጠል፣ የግንባታ ሂደቱን በማስቀጠል ከፍፃሜ የሚያደርሰው ደግሞ የዴሞክራሲ ትውልድ ነው። ይህን ሂደት በአግባቡ ለማስቀጠል ሁለቱ ትውልዶች የኃላፊነትና የሥልጣን ርክክብ ሊያደርጉ ይገባል። ይህ ካልሆነ ግን፣ በአብዮት የተገነባው የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መሰረት በሌላ አብዮት ይፈርስል። የግንባታ ሂደቱ ይቋረጣል፣ የተገነባው መሰረት ፈርሶ፣ ሂደቱ እንደ አዲስ ከዜሮ ይጀምራል። አሁን ባለው ሁኔታ ኢትዮጲያ ወደዚህ አጣብቂኝ እየገባች ነው፤ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ሂደቱን ማስቀጠል ወይም እስካሁን የተገነባውን አፍርሶ እንደ አዲስ ከዜሮ መጀመር።
ለግጭቱ ዋና መነሻ ምክንያት፣ ሜ/ጄ አበበ ተክለሃይማኖት “የእኛ ትውልድ” ያሉት፣ በኢትዮጲያ ዘመናዊ ታሪክ “የአብዮት ትውልድ” የሚባለው፣ ሀገሪቱን የመምራት ኃላፊነትና ሥልጣንን ሙሉ-ለሙሉ ለተተኪው ትውልድ ለማስረከብ ዳተኛ ስለሆነ ነው። በእርግጥ አሁንም በአብዛኛው የአመራር ሚና እየተጫወተ ያለው የ1960ዎቹ ትውልድ ነው። ነገር ግን፣ የአንድ ትውልድ ዘመን አማካይ እድሜ 30 ዓመት እንደመሆኑ፣ የእዚህ ትውልድ ዘመን እስከ 1990ቹ ድረስ ብቻ ነው። ከዚያ በኋላ በሥልጣን ላይ በቆየባቸው አመታት ኮትኩቶ የሚያሳድገው የዴሞክራሲ ቡቃያን ሳይሆን የአምባገነንነት አረምን ነው።
ጭቆናና አምባገነንነትን ታግሎ ለዴሞክራሲ መሰረት ያቆመ አብዮተኛ ትውልድ፣ ከቆይታ ዘመኑ በላይ በስልጣን ላይ በቆየ ቁጥር ራሱን ወደኋላ መልሶ ጨቋኝና አምባገነን ይሆናል። የዳበረ የፖለቲካ ሥርዓት ያላቸው ሀገራትን ተሞክሮ በአንክሮ ላስተዋለ፣ የአብዮት ትውልድ ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ መሰረት ከማቆም ባለፈ ግንባታውን ከጫፍ አያደርስም።
በፅሁፉ መግቢያ ላይ እንደተጠቀሰው፣ ይህ አብዮተኛ ትውልድ በባህሪው ዴሞክራሲያዊ አይደለም። እንደ ሜ/ጄ አበበ አገላለፅ “የአማፂ ትውልድ” እሳቤና አመለካከት ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ግብዓት የሚሆን አይደለም። በአጠቃላይ፣ አብዮተኛ ትውልድ ዴሞክራሲያዊ ትውልድ አንፆ ያሳድጋል እንጂ ራሱን በራሱ ዴሞክራሲያዊ ማድረግ አይቻለውም። በዚህ መሰረት፣ የ1960ዎቹ አብዮተኛ ትውልድ የአሁኑን አዲስ – ዴሞክራሲያዊ ትውልድ ወልዶ አሳድጓል። ይህን ፅንሰ-ሃሳብ በግልፅ ለመረዳት በሁለቱ ትውልዶች መካከል ያለውን መሰረታዊ ልዩነት በዝርዝር መመልከት ያስፈልጋል።
በመጀመሪያ ደረጃ፣ የአብዮታዊ ትውልድ የፖለቲካ እንቅስቃሴ መነሻው ጭቆናና አምባገነንነት ሲሆን መድረሻው ደግሞ እኩልነትና የሕግ-የበላይነትን ማረጋገጥ ነው። ለዴሞክራሲ ትውልድ ፖለቲካ እንቅስቃሴ መነሻው የፍትህና መልካም አስተዳደር እጦት ሲሆን መድረሻው ደግሞ ፍትህና ነፃነትን ማረጋገጥ ነው። የብዙሃን እኩልነት ባልተረጋገጠበት ስርዓት ውስጥ የሚወጣ ሕግ የተወሰኑ የሕብረተሰብ ክፍሎች ጥቅም ከማስከበር የዘለለ ፋይዳ የለውም። ስለዚህ፣ እኩልነት እንዲረጋገጥ ሁሉም ሰዎች እኩል የሚዳኙበት ሕግ ያስፈልጋል። በመሆኑም፣ እኩልነትን ለማረጋገጥ የሕግ የበላይነት መረጋገጥ አለበት። የሕግ-የበላይነት ባልተረጋገጠበት እኩልነት ሊረጋገጥ አይችልም። ለምሳሌ የቀድሞ ዘውዳዊ አገዛዝ የሀገሪቱን ዜጎች እኩልነት ያረጋገጠ አልነበረም። ይህን ሥርዓት በመቃወም የተጀመረው የፖለቲካ እንቅስቃሴ በዋናነት በእኩልነትና የሕግ-የበላይነት መርሆች ላይ የተመሰረተ ነበር።
የደርግ እና ኢሕአዴግ አመራሮች የዚህ ትውልድ አባል እንደመሆናቸው፣ የሁለቱም እንቅስቃሴ ተመሣሣይ ነበር፡- በሀገሪቱ ውስጥ አብዮታዊ ለውጥ በማምጣት እኩልነት እና የሕግ-የበላይነትን ማረጋገጥ። ዘውዳዊ ሥርዓትን በመገልበጥና በዚህም የብዙሃንን እኩልነት በማረጋገጡ ረገድ ደርግ፣ እንዲሁም ሕጋዊ መሰረት ያለው አስተዳደራዊ ስርዓት በመዘርጋቱ ረገድ ደግሞ ኢሕአዴግ ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል። በመሆኑም፣ አሁን በኢትዮጲያ ያለው ሥርዓት ደርግና ኢሕአዴግ በጋራ በወሰዷቸው የለውጥ እርምጃዎች የመጣ ነው። ደርግ በእኩልነት ላይ፣ በተለይ የመሬት ለአራሹ እና የከተማ መሬትና መኖሪያ ቤት አዋጆች የመሳሰሉት፣ እንዲሁም የኢሕአዴግ ሕገ-መንግስታዊ ሥርዓት፣ የአብዮተኛ ትውልዱ የመጨረሻ ግቦች ነበሩ/ናቸው። ይሁን እንጂ፣ እነዚህና የመሳሰሉት የዚያ ትውልድ የለውጥ እርምጃዎች በኢትዮጲያ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ የመሰረት ምንጣፍ ብቻ ናቸው። ይህ ከ1960ዎቹ -1990ዎቹ ባሉት የአንድ ትውልድ ዘመን ውስጥ ተፈፅሟል ማለት ይቻላል፡፡
የአብዮተኛ ትውልድ የመጨረሻ ግብ ለተተኪው የዴሞክራሲ ትውልድ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ መነሻ የሆነ መሰረት ማቆም ነው። ምክንያቱም፣ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መሰረታዊ ዓለማ ፍትህና ነፃነትን ማረጋገጥ መቻል ነው። ሁሉም የሀገሪቱ ዜጎች በእኩልነት በማይዳኙበት ስርዓት ውስጥ ፍትህ ሊኖር አይችልም። በሕገ-መንግስቱ የተቀመጡ፤ በነፃነት የማሰብ፣ የመናገርና የመፃፍ መብትን ማክብርና ማስከበር፣ እንዲሁም ሌሎች ዴሞክራሲያዊ መብቶችን ማረጋገጥ እስካልተቻለ ድረስ የሕግ-የበላይነት ሊረጋገጥ አይችልም።  ፍትህና ነፃነትን በሌለበት እኩልነትና የሕግ-የበላይነት ትርጉም አልባ መፈክሮች ናቸው። በመሆኑም፣ በአብዮት ትውልድ የእኩልነትና የሕግ-የበላይነት ያረጋገጥ እንጂ የመጨረሻ ግባቸው ግን ፍትህና ነፃነት ነው።
የአብዮት ትውልድ ፖለቲካ የዴሞክራሲያዊ ስርዓት መነሻ ነው። የዚህ ትውልድ እንቅስቃሴ ዓላማው ግን ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን ማረጋገጥ ነው። የአብዮት እንቅስቃሴ ሲጀምር “የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች እኩልነትና የሕግ-የበላይነት ይረጋገጥ” የሚል መፈክር ይዞ ነው። የዚህ ዘመን ትውልድ ግን የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች እኩልነትን ተቀብሎ እና በሕግ-የበላይነት አመኖ፣ “ፍትህና ነፃነት ይከበር!” ብሎ ነው። የአብዮት ትውልድ እንቅስቃሴ የጀመረው “እኛ” በሚል እሳቤ ነው። አሁን ያለው የዴሞክራሲ ትውልድ እያነሳ ያለው ጥያቄ ግን “እኔ” በሚል እሳቤ ነው። “የእኛ” ጥያቄ የቡድን መብትን ስለማክበርና ማስከበር ነው። በቡድን መብት ውስጥ የእኛ፤ የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች የእኩልነት እና ይህን ለማረጋገጥ አስፈላጊ የሆነው የሕግ የበላይነት ይዘረጋል። “የእኔ” ጥያቄ የግለሰብ መብትን ስለማክበርና ማስከበር ነው። በግለሰብ መብት ውስጥ ፍትህና ነፃነት ይረጋገጣል። “እኛ” ብሎ የተነሳው ትውልድ መነሻ ግቡ አሮጌውን ሥርዓት በማፍረስ፣ መንግስታዊ መዋቅሩን በመቀየር የብዙሃንን እኩልነትና የሕግ-የበላይነትን ለማረጋገጥ ነው። “እኔ” ብሎ እየጠየቀ ያለው አዲሱ ትውልድ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን ለመገንባት የተነሳ ነው። ጥያቄው የመዋቅር ለውጥ ሳይሆን የአስተዳደራዊ ሥርዓቱን ማሻሻል ነው።
የአዲሱ ትውልድ ትግል ለድንገታዊ አብዮት ሳይሆን የዳበረ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን ለመገንባት ነው። የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታን ለማስቀጠል፣ በሁሉም የሕይወት ዘርፎች ለውጥና መሻሻል እንዲኖር፣ የአብዮቱ ትውልድ ሀገሪቱን የማስተዳደር ሙሉ ሥልጣንና ኃላፊነት ለአዲሱ ትውልድ ማስረከብ አለበት። ነገር ግን፣ ላለፉት አስር አመታት እንደታየው፣ የአብዮቱ ትውልድ ሥልጣንና ኃላፊነቱን ለማስረከብ ፍቃደኛ አይመስልም። በዚህ ምክንት፣ በሁለቱ ትውልዶች መካከል ግጭት ተፈጥሯል። የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ሂደቱን የሚያቋርጥ፣ እስከ አሁን የተገነባው መሰረት የሚያፈርስ ግጭት ተፈጥሯል። በአጠቃላይ፣ ግጭቱ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን የማስቀጠል ወይም የማቋረጥ ጉዳይ ሆኗል።

ደርግነት እያቆጠቆጠ - ዴሞክራሲው እየጨላለመ ነው - ህዝቦች ጠንቀቅ በሉ! (ሜ/ጄ አበበ ተክለሃይማኖት)

ደርግነት እያቆጠቆጠ - ዴሞክራሲው እየጨላለመ ነው - ህዝቦች ጠንቀቅ በሉ! (ሜ/ጄ አበበ ተክለሃይማኖት)

አበበ ተክለሃይማኖት(“ጆቤ”)
(ሜጀር ጄኔራል፣ PhD Candidate)
መግቢያ
የሃገራችን መንግስትና የገዢው ፓርቲ አጠቃላይ ችግር ዉስጥ በመግባታቸው ምክንያት እዚህና እዝያ እሚታዩ ችግሮች እየተስተዋሉ ነው። ሰሞኑን እንዃ ብናይ ከኦሮሞ ህዝባዉ ዓመፅ፣ ሜቴክና ስዃር ፋብሪካ፣ ከጋምቤላ ጠለፋና ግድያ፣ በኤርትራ በኩል የሚመጣ ተከታታይነት ያለው ዜጎቻችንን የማበሳበስ ሁኔታ እያስተዋልን ነው። የድርቁና በየክልሉ የሚታዩ የህዝቦች መነሳሳት ተጠቓሽ ናቸው። እነዚህ የሚፈጠሩ ነገሮች ካጠቃላይ ሕገ መንግስታዊ ማእቀፉና ከህዝቦች ፍላጎት አንፃር ማየት አለብን።
አንድ ጏደኛየ “ህወሓት የለችም ማለት የትግራይ ህዝብ የለም ማለት ነው፤ ስለዚ ህወሓት ማለት ህዝብ ነው፤ ኢህአዴግ ማለት ደግሞ የኢትዮጵያ ህዝብ ማለት ነው” ማለት ምን ማለት ነው ብሎ ጠየቀኝ። እኔም እንዲህ ብሎ ነገር የለም ከየት አመጣሀው አልኩት፤ እሱም የሃገራችን ኢታማዦር ሹሙ ናቸው የተናገሩት አለኝ በትግርኛ የግንቦት ሃያ ስብሰባ ላይ መቐለ ከተማ የተናገሩት ብሎ ሊንኩን ሰጠኝ:: ቪድዮው የ ሶስት ሰዓትና ሃያ ሁለት ደቂቃ ርዝመት ያለው ስለሆነ፤ ይህንን ሁሉ ለማየት ግዜም ፋላጎትም ላይኖራቹህ ስለሚችል ከ2ሰዓት እና 23 ደቒቃ ( 2:23)ጀምራቹህ እንድትመለከቱት እጋብዛለሁ።
ባለፈው ፁሁፌ እንደገለፅኩት የወታደራዊ ክፍሉ ጡንቻ እየፈረጠመ የመሄዱ አዝማምያ ያሰጋኝ እንደነበር ገልጬ ነበር። ይህንን ቪድዮ ሳየው ግን ወታደራዊ ታልቃ ገብነቱ ከምገምተው እና ከጠበቅኩት ፍጥነት በላይ ሆኖ ሳገኘው ደርግነት ተመልሶ እየመጣ ይሆን እንዴ? ብየ ለመጠየቅ ተገደድኩ።የዴሞክራሲ እጥረት ወይም ምህዳር መጥበብ ማለት ደርግነት መንገስ ማለት ነው፤ ሱፍም ወታደራዊ ልብስም ሊለብስ ይችላል።
Photo - Major General Abebe Teklehaimanot
Photo – Major General Abebe Teklehaimanot
ደርግነት ምንድን ነው?
ደርግነት ወታደራዊ ክፍሉ ፖለቲካዊ አመራር ከኔ በላይ የሚችለው የለም ብሎ ስልጣን መቆናጠጥ ነው። ደርግነት ሁሉም ዴሞክራስያዊ መብቶች በሃይል ለማፈን የሚደረግ አስተሳሰብ እና ድርጊት ነው። ደርግነት የኢትዮጵያ ህዝቦች አንገዛም ማለት ሲጀምሩና ፖለቲካዊ አመራሩ መምራት ሲያቅተው ወታደራዊ ክፍሉ ድሮስ ከኔ በላይ ማን አለ በሚል ትዕቢት ጠብመንጃ ቤተ መንግስትን ሲቆጣጠር ነው። ደርግነት ሲጀምር “የህዝብ ጥያቄ ለመመለስ ምርጥ ልጆቹ እንደተሰበሰቡ”  ለማሳየት እንቅስቃሴ ማድረግ ነው። ደርግነት የ “አንድ ህዝብ፣  አንድ ፓርቲ፣ አንድ መሪ”  የሚሰብክ ፀረ ዴሞክራሲያዊ አስተሳሰብና ተግባር ነው።
ደርግነት አንድ ህዝብ፣ አንድ መንግስት (One State)፣ አንድ መሪ (führer) የሚለዉን የናዚ አስተሳሰብ ተቀጥያ ነው። በኢትዮጵያም አንድ ህዝብ፣ አንድ ፓርቲ (ኢሰፓ) አንድ መሪ (መንግስቱ ሃይለ ማርያም) እንደ ማለት ነው።  በዘመናችን ደግሞ የኤርትራው ዲክቴተር እንደሚሉት “አንድ ህዝብ፣ አንድ ልብ፣ የራሳቸው አንድ የፖለቲካ ድርጅት፣ ራሳቸው ብቸኛና አንድ መሪ”፤ ከዚህ ዉጪ ያለ መሪም ሆነ ድርጅት የኤርትራ ጠላት አድርጎ የመመልከት አስተሳሰብ ነው ደርግነት። ደርግነት አለመተማመን ነው፤ አንዱ ሌላዉን የሚያሸማቅቅበት ሰርዓት ነው። ፕሬዝዳንት መንግስቱ ሃይለማርያም ቢሆኑም በመፈንቅለ መንግስት ስልጣናቸው እንዳይወሰድባቸው ተሸማቅቀው የሚሮሩበት ነው። ደርግነት ኔትዎርኪንግ ነው፤ መጠላለፍ ነው።
የፈለገ ዓይነት ችግር ቢመጣ “ያው አፍሪካዉያን ስለሆንን በወታደር እንፈታዋለን” የሚል አስተሳሰብ የደርግነት ሀሁ ነው።ፖለቲካዊ መፍትሄ የማይታየው፣ ጭንቀት የፈጠረው ገር አስተሳሰብ ወይም ሁን ተብሎ ጠባብ ጥቅምን ለማስጠበቅ የሚሰነዘር ሃሳብ ነው።ህዝብን በጉልበት እንደሚነዳ እንስሳ የሚቆጥር ኃላ ቀር አስተሳሰብ ነው። ለመጨቆን የሚደረግ መንገድ ጠረጋ ነው። ለአፈና የሚደረግ መንደርደር ነው፤ ባጭሩ የደርግነት መነሻ ነው። የኣፍሪካዊ ሰው ሰብኣዊ እኩልነት አለማመን ነው፤ የቀኝ ገዢ አስተሳሰብ ነው። አይደለምና በደሙ ደርግነትን ያሸነፉት ለኢትዮጵያ ህዝቦች ለማነኛዉም የሰዉ ፍጡር በወታደር የሚሽከረከር ሃገር ኣልመኝም፤ ምክንያቱም ሕገ መንግስታዊና ዴሞክራስያዊ ስርዓት ለመገንባት እከል ስለሚሆን። ለራሳቹህ ጠባብ ጥቅም ለመጠበቅ ስትሉ  “ኢትዮጵያዉያንን በጉልበት ነው መግዛት” እያላቹህ ወታደራዊነት እምታቀነቅኑ ፀረ ሕዝብና ፀረ ዴሞክራሲ መሆናቹህን መገንዘብ አለባቹህ፤ የኢትዮጵያ ህዝቦች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎችና የሲቪል ማህበረሰቡ ይህንን ክፉና አደገኛ አስተሳሰብ በንጭጩ ለመቅጨት መታገል አለበት።  
ደርግነት ተሻንፊነት ነው። ደርግ በጥቁር አፍሪካ አለ የሚባል ስመ ገናና ጦር ይዞ፣ በክፍተኛ ደረጃ የሰለጠኑ መኮንኖች አስልፎ፣ የራሽያ ሙሉ ድጋፍ እየተቸረው በኢትዮጵያ ህዝቦች ፊት ግን ተሸናፊ ሃይል ከመሆን አልዳነም። ለምን ቢባል የፈለገ ወታደራዊ አቅም ቢያዝ ፖለቲካዊ ምክንያት እና ሰልፍ ነው የሚያሸንፈው፤ የደርግ ጠብመንጃም በፍትሕ ፈላጊ ኢትዮጵያዉያን ፖለቲካ ተደመሰሰ። ደርግነት ፀረ ህዝብነት ነው፤ የንቀት እና የማንቛሸሽ ስርዓት ነው።
ውቅታዊ የኢትዮጵያ ፖለቲካና ደርግነት
የኢትዮጵያ ህዝቦች ከህግ ዉጪ አንገዛም ማለት ጀምረዋል። የኦሮሞ ህዝቦች ዴሞክራስያዊ እንቅስቃሴ፣ የቅማንት ህዝቦች ዴሞክራስያዊ ትግል፣ በትግራይ ደግሞ እንደ እምባሰነይቲ ዓይነት ዴሞክራስያዊ እንቅስቃሴ፣ የኮንሶ ህዝቦች ዴሞክራስያዊ ጥያቄን እንደ ምሳሌ ሊወሰዱ ይችላሉ። ገዢው ፓርቲ ቆሟል ወይም ወደ ኃላ እየነጎደ ነው፤ ባጭሩ ጥልቕ ፖለቲካዊ ችግር (political crisis) አለ። ሆኖም ይህንን ችግር መፈታት ያለበት ህገ መንግስታዊ በሆነ መንገድ እንጂ ከዛ ዉጪ በሆነ መንገዶች መሆን የለበትም።
ኢህአዴግ ዉስጣዊ ቐዉስ አጋጥሞታል፤ ወታደራዊ ክፍሉ የአመራር ክፍተትን ለሞሙላት ምን እያደረገ ነው? የሚለው ማየት ተገቢ ነው። በተለያዩ መጣጥፎቼ የዴሞክራሲ እጥረት (democratic deficiency) በሚኖርበት ሁኔታ ሕገ መንግስታዊ ተቛሞች ልፍስፍስ በሚሆኑበት ግዜ ባለጠመንጃው ሁለት ሶስት ግዜ ማስብ ይጀምራል ብየ ነበር፤ የተወሰኑ ምልክቶችም ጠቁሜ ነበር። እንደኛ ባሉ በሽግግር ላይ በሚገኙ ማህበረሰቦች፤ የዴሞክራሲና ሕገ መንግስታዊ ተቛሞች ተገቢ ስራቸዉን መስራት አለመቻላቸው ለጉልበተኛ አካል እድል መስጠታቸው ያገራችን ህልዉናና የህዝቦችን ዋስትና ሲፈታተን ይታያል። ከዚህ አንፃር አሁን ማየት የምፈልገው ወታደራዊ ክፍሉ እያሳየ ስላለው የፖለቲካዊ ፍላጎት ጭላንጭል ነው።
ፖለቲካዊ ሚና የማይኖረው ሕገ መንግስታዊ ተልእኮዉን ብቻ የሚወጣ የመከላከያ ሃይል ለመገንባት የኢትዮጵያ ህዝቦች ከፍተኛ መስዋእትነት ክፍለዋል። የሲቪሉን አስተዳደር ህዝባዊ ስልጣን አክብሮና ለሕገ መንግስቱ ተገዢ ሆኖ ግዴታዉን የሚፈፅም፣ አገሩን በብቃት የሚከላከል፣ ጥቃትን የሚያስቀር ወይም በቂ ምላሽ መስጠት የሚችል ሃይል ሆኖ መገኘት ነው መሰረታዊ ተልእኮው። አሁን ግን በከፍተኛ አመራሮቹ እየታየ ያለው ነገር አንዳንድ ስጋቶችን እየጫረ ይገኛል።
የመቐለው ፓናል
በቅርቡ ኢታማዦር ሹሙ ጄኔራል ሳሞራ የኑስ ግንቦት ሃያን አስመልክተው በመቐለ ከተማ ያካሄዱት ዉይይት ላይ ያነስዋቸው ሃሳቦችና እና የተናገርዋቸው ነገሮች በጣም እሚያሳዝኑና ሕገ መንግስቱን ገድል ግባ ያሉበት መድረክ ነበር። ከ ሀ እስከ ፐ  ስለ ሲቪል አስተዳደሩ ድክመት፣ ልፍስፍስነት፣ ስለ ወታደራዊ ክፍሉ የመተካካት ልዩ ችሎታና ስለ ሰራዊቱ የአሁንና የወደፊት ጥንካሬ ሲያወሩ ላየ ጄኔራሉ ምን እያለ እንደሆነ ይገባዋል ወይ? የሚል ጥያቄ ያጭራል። “ፖለቲካዊ አመራሩ እንጂ ወታደራዊ ክፍሉ ጤነኛ ነው” እሚል መልእክት አደገኛ አካሄድ ነው፤ እኔ ልምራ አይነት አንደምታ ያለው ንግ ግር ነው። የሲቪል መንግስት በወታደራዊ ክፍሉ የሚገመገምበት አሰራርም ሆነ ሕገ መንግስታዊ መርህ ወይም ድንጋጌ የለም። ሲቪል አስተዳደሩ ወታደሩን ሊቆጣጠር ሲገባው በተገላቢጦሽ ወታደራዊ ክፍሉ ሲቪሉን አትረባም፣ ሞተሃል፣ አመራር አታዉቅም እያለው ነው።
ሲጀመር ስብሰባው ምን አላማ ታሳቢ አድርጎ በማን ለምን እንደተዘጋጀ መጠየቅ አለበት። እዉነት የግንቦት ሃያ መንፈስ ለማስረፅ ነው የተዘጋጀው? የግንቦት ሃያ መንፈስ ሕገ መንግስታዊ መርሆችና ድንጋጌዎች እየተጣሰ ነው እንዴ እሚከበረው? ሕገ መንግስቱን በግላጭ እየደረመሱ ግንቦት ሃያን ማክበር ብሎ ነገር አለ እንዴ? በዶከተር ዛይድ አወያይነት የተጀመረው የሁለቱ ንግግር ከ 1967ዓ.ም እስከ 1983 ዓ.ም የነበረዉን ፖለቲካዊና ወታሃደራዊ ሁኔታ በዝርዝር አስቀምጠዋል። አሁን ስላለው ፖለቲካዊን ችግሮች ሁለቱም ለየቅልና ተቃራኒ ሓሳቦች አስቀመጡ፤ ኢታማዦር ሹሙ በዚህ ጉዳይ መግባት ባይኖራቸዉም።
አቶ ኣባይ ፀሃየ አሁን ያሉት ፖለቲካዊ ችግሮች የዴሞክራሲ እጦት፣ የሙስና መስፋፋት እና የበላይ አመራሩ እርስበርሱ አለመታገል (አድርባይነት) ነው አሉ። መፍትሔዉም ዴሞክራሲን ማስፋፋት እና በዚህ እና በመልካም አስተዳደር ያሉትን ችግሮች የበላይ አመራሩ ያለ ማቅማማት መታገል ነው አሉ። ጄኔራል ሳሞራ ደግሞ የችግሮቹ ምንጭ ኪራይ ሰብሳቢነትና ዕድገት ነው አሉ። መፍትሔ ሲጠቁሙ ደግሞ አቶ ኣባይ ያሉትን በመፃረር ወይም የኣቶ አባይ መነሻ ሃሳብና መፍትሔ ገሸሽ በማድረግ ላይኛዉ አመራር ፕሮጀክት መምራት እና በቴሌቭዥን መታየት ስራው በማድረግ በቦታው አለመገኘቱ ነው አሉ። የፖሊሲ፣ የመመርያ፣ የአሰራር ችግሮች ዋነኞቹ ችግሮች ናቸው በሚል ያለዉን ፀረዴሞክራሲ አስተሳሰብ ለማድበስበስ ሲፈላሰፉ ታይቷል።
አመራር ማለት ፕሮጀክቶች መምራት እና በቴሌቭዢን መታየት አይደለም ብለዋል ጄኔራሉ፤ ማንን ለመምታት ይሆን? የሚለው መጠየቅ ተገቢ ነው። ሲጠቃለል የኢህአዴግ መንግስት ችግር አቶ ኣባይ ፀሃየ እንዳስቀመጡት ነው ወይስ ጄኔራሉ እንዳሉት? የአቶ አባይ ፀሃየ ፖለቲካዊ ግምገማ በጄኔራሉ ሲቪል አስተዳደሩን የማንቛሸሽ ንግግር ታጅቦ የቀረበበት ፖለቲካዊ ምክንያት ምንድን ነው? ማን ምን ቢፈልግ ነው እንዲህ አይነት ዘመቻ የተጀመረው? የሚል ጥያቄ የሚያስነሳ ነገር ነው እየታየ ያለው።
ከሁሉም በላይ የሰቀጠጠኝ ነገር ግን ስለ ኢትዮጵያ ህዝብ ባጠቃላይ ስለ ትግራይ ህዝብ ደግሞ በዋናነት ያሉት ነገር ነው። ለሳቸው የትግራይ ህዝብ ማለት ህወሓት ነው፤ የኢትዮጵያ ህዝብ ማለት ደግሞ ኢህአዴግ ነው። ህወሓት/ኢህወዴግ የለም ይባላል እርስዋስ ምን ይላሉ ተብለው ሳይተየቁ በራሳቸው አነሳሽነት የሃገር ኢታማዦር ሹም ምን እንዳለ ላካፍላቹህና አሉና “አንዳንድ ሰዎች ህወሓት የለም ይላሉ ፤ እንዲህ እሚሉት ሰዎች ራሳቸው ላይኖሩ ይችላሉ። ለኔ ህወሓት ማለት መስመር ነው፣ ህወሓት ማለት ህዝብ ነው፣ ሌላ አይደለም። እኔ የሚገባኝ ህወሓት የለችም ማለት የትግራይ ህዝብ የለም ማለት ነው፤ ስለዚ ህወሓት ማለት ህዝብ ነው፤ ኢህአዴግ ማለት ደግሞ የኢትዮጵያ ህዝብ ማለት ነው” ብለው ተናገሩ
በዘመናት የትዉልድ ቕብብሎሽና ዉርስ ታሪኩና ማንነቱ በክብር ያቆየዉን የኢትዮጵያ ህዝብ በዚ መልኩ ወደ ድርጅት ጀረጃ አውርዶ ማሳነሱ ሳይበቃ የዚህ ኩሩ ህዝብ ህልዉና በፖለቲካዊ ድርጅቶች ሲረጋገጥ የቆየ ይመስል ኢህአዴግ የለም ማለት የኢትዮጵያ ህዝብ የለም ማለት ነው ብሎ ንግግር ክትዕቢት (Arrogance) እንጂ ከሌላ ሊመነጭ አይችልም። ህወሓት ሆነ ኢህወዴግ እንደ መድረክ ወይም ኢዴፓ ወይም ሌሎች ፓርቲዎች አንድ የፖለቲካ ድርጅት እንጂ የትግራይን ወይም የኢትዮጵያን ህዝብ መተካት የሚችሉ የህዝብ አቻ የሆኑ መዋቅሮች አይደሉም። ሲጀመር የሚያደጉት ነገር ከሕገ መንግስት አንፃር ምን ማለት እንደሆነ ሳይገባቸው ቀርቶ ነው?
ህወሃት ማለት የትግራይ ህዝብ ነው የሚለው አነጋገር ፀረ ህዝብነቱ የሚጎላው ፀረ ሕገ መንግስታዊ ይዘቱ ስንረዳ ነው። ህብረ ፓርቲነት በሕገ መንግስትዋ ያወጀች አገር ፣ ለዛዉም በስንት መስዋእትነት በመጣ ሕገ መንግስት፣ አንድ ኢታማዦር ብድግ ብሎ ህወሓት ማለት የትግራይ ህዝብ ነው፣ ኢህአዴግ ማለት ደግሞ የኢትዮጵያ ህዝብ ነው ሲል ያሳፍራል። የትግራይ ህዝብ ህወሓትን ፈጠረ እንጂ ህወሓት የትግራይ ህዝብን አልፈጠረችዉም።
የትግራይ ህዝብ የጋራ የሆነ ፍላጎቶችና ክብሮች ቢኖሩትም ሁሉም ነገሩ ግን አንድ አይደለም። የትግራይ ህዝብ ስንል ገበሬው፣ ላብአደሩ፣ ተማሪና ሙሁሩ፣ ባለሃብቱ እና ወዘተ ነው። የትግራይ ህዝብ ስንል ክርስትያኑ፣ እስላሙ፣ ኩናማው ፣ኢሮቡ ፣ ወጣቱ፣ ሽማግሌው፣ ሴት፣ ወንድ ነው። የተለያየ ፍላጎትና እሴቶች አሉት። ብዙሃነትን የሚያስተናግድ ህዝብ ነው። እነዚህ የተለያዩ ጥቅሞችና እሴቶች የተለያየ መስመርና አደረጃጀቶች ሊተይቅ ይችላል። የተለያዩ ድርጅቶች ሊከሰቱ ይችላሉ፤ ከሁሉም በላይ ግን አንድ መስመር የሚሉት ፀረ ዴሞክራሲ አባዜ ነው። ጥቂት የተመረጡ የበላይ አመራሮች ለህዝብ የሚጠቅመው ይህ ነው ማለታቸው ብቻ በቂ አይደለም ። የትግራይ ህዝብ ስለ ህወሃት ምን እንደሚል የህወሓት የንደፍ ሃሳብ ልሳን የሆነዉን <ወይን< ምን እንደሚል እስኪ ያንብቡት።
የአገር መከላከያ ኢታማዦር ሹም በጠራራ ፀሃይ የሕገ መንግስቱ አንቀፅ 87 ( 87/4የመከላከያ ሰራዊት በማናቸዉም ግዜ ለሕገ መንግስቱ ተገዢ ይሆናል 87/5 “የመከላከያ ሰራዊት ተግባሩን ከፖለቲካ ድርጅቶች ወገናዊነት ነፃ በሆነ ኣዃሃን ያከናዉናል”) እና ሌሎች ሕጎችን በመፃረር ለህወሓት ጥብቅና መቆም ምን ይባላል? ህወሓት ልክ እንደ ሌሎች የኢህአዴግ ድርጅቶች ያለዉን ቀዉስ አንዱን ወገን ደግፈው በመንግስት ገንዘብ ጊዜ ኮኮብ እየሰሩ ነው እኮ። እነዛ የተደረደሩት ኮኮቦች ሕገ መንግስቱን መጣስ ሲጀምሩ አፈር እንደሚሆኑ ዘነጉት እንዴ? በህወሓት ዉስጥ እርስዎ የሚደግፉት ወገን ህወሓት የለችም ማለት የትግራይ ህዝብ የለም ማለት ነው የሚል ከሆነ እንጦርጦሱ ይግባ።
የሁለት ትዉልዶች ወግ
ጄኔራል ሳሞራ ህወሓት የለችም የሚሉ ምናልባት ራሳቸው የሌሉ እንዳይሆኑ ካሉ በኃላ፤ በጉባኤው ተሳታፊ የነበረችው ወዛም ታደለ የተባለች አምስተኛ ዓመት የህግ ተማሪ “እኔን ጨምሮ ኣብዛኛው ወጣት ህወሓት የለም እምንለው መሬት ላይ ካለ የመልካም አስተዳደር ችግር ተነስተን ነው፤ ብዙ ነገር ጠብቀን እምንፈልገው ነገር ስለማናገኝ ነው፣ ስለዚህ የህወሓት ህልዉና ከዚ ጋር ኣያይዘው እንዲገነዘቡት ነው እምፈልገው” ብላ ትምህርት ስጥታ ጥያቄዋን ሰነዘረች። ጀግና ወጣት ናት!
ጄኔራሉ ህወሓት አለች ምክንያቱም የትግራይ ህዝብ አለ ሲሉ ጅግናዋ ልጂትም አይ ለኔ ህወሓት እምገነዘባት መሬት ላይ ካለ የመልካም አስተዳደር ሁኔታ ጋር ነው፤ ከመንግስታዊ ድርጊት ጋር ነው ብላ “በዚ መልኩ ሊገነዘቡት ይገባል” ብላ ታሪክ የማይረሳው ትምህርት ስጥታለች። በተማረው ወጣቱ ትዉልድ ያለኝኝ ተስፋ በተማሪ ወዛም ታደለ በኩል ማየቴ ብኮራም፤ በስልጣን ላይ ባለዉ ትዉልድና በሚመራው ትዉልድ መሃል ያለው የመረዳትና የእዉቀት ልዩነት ግን የሰማይና የምድር ያህል መራራቁ ግልፅ ያደረገ መድረክ ነበር።
ግለሰቦች ተቛምና የሃገር ደህንነት
የሜቴክ እና የመከላከያ ዕቃ ግዢ ግንኙነት ያላቸው ሰዎች የመልካም አስተዳደር ችግር ያለው በሲቪል መንግስት ብቻ ነው፤ መከላከያው ግን በጣም ጠንካራ ነው እያሉ ፕሮፖጋንዳ ይነፋሉ። ጄኔራሉም የዚህ ፕሮፖጋንዳ ሰለባ ሆነው መከላከያን እያንቆለጳጰሱ ለአሁኑም ለወደፊቱም እንደተዘጋጁ ሲነግሩን የመንግስት ከፍተኛ የፖለቲካ አመራሩን ደግሞ ትምህርት ቤት ክፍተው ስለ አመራር ለማስተማር የተዘጋጁ ይመስላሉ::
በዚህ ጉዳይ ከኣንዳንድ ሰዎች ጋር ስነጋገር ጄኔራል ሳሞራን ኣትንካ፤ የአገራችን አለኝታ ናቸው። ያለሳቸው መከላከያዉም ብሎም አገራችን ችግር ዉስጥ ትገባለች አሉኝ፤ ምን ማለት ነው? ሕገ መንግስቱና ሕገ መንግስታዊ ስርዓቱን በግላጭ ሲጥሱስ ብየ ጠየቅዃቸው። <ቢሆንም ይሁን< ነበር መልሳቸው።
በትጥቅ ትግል ግዜ ከጀግኖች መሪዎች አንዱ ነበሩ፤ በኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ም ቢሆን እንደ ፊልድ ኮማንደር ልዩ አስተዋፅኦ ነበራቸው፤ ጦርነቱ ተንገራግጮ ከዚህ በላይ መቀጠል ኣንችልም እስኪባል ድረስ። ጀግና የነበረ ሁል ግዜ ጀግና፤ ለህዝብ ተቆርቛሪ የነበረ በቀጣይነት እንደዛ ይሆናል ባይባልም ከፈተኛ ክብር ግን ይገባቸዋል። ነገር ግን የኢትዮጵያ ህዝቦች የተዋደቁለትንና በብዙ መስዋእትነት እዉን ያደረጉትን ሕገ መንግስትና ስርዓቱን በግላጭ ሲንዱ ተው መባል አለባቸው።
የኔ ተስፋ መከላከያ ተቛማዊ አስራር ገንብቶ ማንም መሪ ቢሄድ ቢመጣ ስርዓቱን ተከትሎ የሚሄድ ጠንካራ መዋቅር ሆኖ ማየት ነው። ካልሆነ ግን በግለሰቦች እሚንጠለጠል ተቛም ተሁኖ ይህን አገር መከላከል አይቻልም።
ከአስራ አምስት አመት በላይ የአገር መከላከያ ኢታማዦር ሹም ሆነው ሲያገለግሉ፣ ብዙ ጀግኖችና ብቃታቸው ያረጋገጡ ከፈተኛ መኮንኖች የነበሩት መከላከያ እሳቸው ከተነሱ አደጋ ዉስጥ የሚገባ ከሆነ እማ አስራ ኣምስት ዓመት ጥፋት ሲፈፅሙ ነበር ማለት ነው፤ እሳቸው በሌሉበት እንደ ተቛም የበለጠ ተጠናክሮ የማይሰራ ከሆነ ይች አገር በእዉነትም አደጋ ላይ ነው ያለችው።
ከዚህ ጋር የተሳሰረ ወጣቶች ያወጉኝን ላካፍላቹህ።የስዃር ኮርፖሬሽን አመራሮች ፓርላማ ቀርበው “ያሸማቁቁናል፣ ሜቴክን መቅጣት እንደማንችል ሁላቹሁም ይገባቹሃል” ባለቡት ሳምንት ሁለት ወጣቶች አግኝቼ ከሌሎች ሁሉት ጏደኞቻቸው ሆነው ሁለት ለሁለት ተከፍለው በዚህ ዙርያ የጦፈ ክርክር ማድረጋቸው ነገሩኝና ስለምን? ብየ ጠየቋቸው። ሁሉም የተማሩ ወጣት የትግራይ ልጆች ናቸው። ዉይይታቸው ፓርላማ ሜቴክን እንደዛ መጠየቁና ብልሹ አስራር መታገል እንዳለበት ቢስማሙም በተወሰነ ነጥብ እንደተለያዩ ነገሩኝ። ሁለቱ ወጣቶች እዉነታው አሳዛኝ ቢሆንም ኣላማው ትምክህተኞች ትግራይን ለመጉዳት ሆነ ብለው ያቀነባበሩት ሴራ ስለሆነ ከሚጮሆም ጋር ኣብረን መጮህ የለብንም ሲሉ የተቀሩት ሁለቱ ወጣቶች ደግሞ የለም በሴራ ሃሳብ ገብተን ሌብነትን ከብሄር ጋር እያገናኘን እማይገባቸው ከለላ መስጠት የለብንም፤ እንደዉም ለፍትህ መቅረብ አለባቸው፤ ሜቴክም አጠቃላይ አሰራሩ መፈተሽ አለበት ብለው እንደሞገትዋቸው ከሁለቱም ጎራ የነበሩ ሁለቱ ወጣቶች ነገሩኝ።
ሜቴክ አመራር ላይ በርከት ያሉ የትግራይ ተወላጆች ሊኖሩ ይችላሉ። በትግራይ ይሁን በሌላው ኢትዮጵያ እንደ ትግራይ ተቛም አድርጎ ማየቱ ( percieve  ማድረጉ) መሰረታዊ ስህተት ነው። ሜቴክ የቴክኖሎጂ ማእከል የኢትዮጵያ ሽግግር (Transformation) ሻምፒዮና የሚሆንበት ሂደት እንደ ትግራይ/ኢትዮጵያ ሁላችንንም ሕገ መንግስቱ ማእከል አድርጎ ተጠያቂነት፣ ግልፅነት፣ የሕግ የበላይነት ያለንን የሰው ሃይል እና በመቶ ቢልየኖች ቆጥቦ ሲሰራ እንኮራበታለን። እጅጉን እናመሰግነዋለን።
ሜቴክ ተጠያቂነት፣ ግልፅነት፣ የሕግ የበላይነት የማይመለከተው አካል ሆኖ የአገራችንን ከፍተኛ ሃብት ሲያጠፋፋ ግን እንደ ኢትዮጵያዉያን ራሳችንን ደፍተን እናዝናለን። እዛ ያሉ የትግራይ ተወላጆች ጥቂት ቀጣፊዎችና ከነሱ ጋር የሚቀራረቡትን ይጠቀማሉ እንጂ የትግራይ ህዝብን እየበደሉት ነው፤ ለዛዉም ባለ ሁለት ስለት በደል። ባንዱ በኩል እንደ ማንኛዉም ኢትዮጵያዊ የሃገራቸው ሃብት እየተዘረፈ ነው፤ በሌላ በኩል በስሙ እየነገዱ ነው፣ ሌሎች ብሄር ብሄረሰቦች ደግሞ ወደ አላስፈላጊ ጥርጣሬ እንዲገቡ ሊያደርግ ይችላል።
ከየትኛዉም ብሄር ብሄረሰብ ወይም ህዝቦች ሕገ መንግስትን፣ ፖሊሲዎችንና ሕጎችን አክብረው በተጠያቂነትና ግልፅነት ቀንና ሌሊት ሰርተው አገራችንን በመለወጥ የድርሻቸዉን ሲወጡ እደጉ ተመንደጉ እንደምንለው ሁሉ፤ ከዚህ በተፃራሪ የሚሰሩትን ቀጣፊዎችን ደግሞ ቀጣፊዎች እንበላቸው አልዃቸው።
ስዃር ኮርፖሬሽን እና ሜቴክ በሚመለከት ጉድ የተባለለት ሪፖርት “ሾልኮ” ለፓርላማና ለህዝቡ ተገልፆ መወያያ በሆነበት ግዜ እና ፓርላማው የመጨረሻ ዉሳኔ ባልሰጠበት ሁኔታ የመንግስት ልማት ድርጅቶች ቛሚ ኮሚቴ እያንዳንዱ በሜቴክ ተቛሞች እየተዘዋወረ ምስጋና እየደረደረ ነው። የሚገባቸው ከሆነ ይበል የሚያስብል ነው። ግን ደርግነት መንገስ በጀመረበት ከባቢ (Environment) ቛሚ ኮሚቴው ተሸማቆ ይሆን እንዴ እንዲህ የሚያደርገው> የሚል ጥያቄ ሰዎች ያነሳሉ።
መደምደምያ
ደርግነት በሁለት ኢ-ሕገ መንግስታዊና ስርዓት-የለሽ በሆነ መንገድ ሊከሰት ይችላል።አንደኛው በግላጭ መፈንቅለ መንግስት ማድረግ ነው። ሁለተኛው የህወሓት ማእከላይ ኮሚቴ ብሎም የኢህአዴግ ምክር ቤት ወይም ፈፃሚዉን መመርያ በመስጠትና በማስፈራራት “እከሌ ሊቀ-መንበር እንዲሆን እከሌን አዉርዱት” ወዘተ በማለት ሊሆን ይችላል። በድርጅቱ ባለው ሁኔታ ይህ አይቻልም ማለት የዋህነት ነው። የግንቦት ሃያ በዓል አስመልክቶ የተደረገው ፓነል ይህን ለማስረገጥ እንዳይሆን መጠንቀቅ አለብን። ኢህአዴግ ዉስጥ ያለው ችግር ባልተመሰቃቀለና ሕገ መንግስታዊ በሆነ መልኩ ከህዝቦች እና ሌሎች ፓርቲዎች ተሁኖ መፈታት ያለበት ጉዳይ ነው፤ ያለ ምንም የወታደር ጣልቃ ገብነት።
የኢትዮጵያ ሰላም፣ ልማት እና ዴሞክራሲ በ ህዝቦች ተሳትፎ እና ትግል ስ ለሚረጋገጥ ሁሉም ሰው መታገል አለበት። ትልቁን የኣሜሪካን መንግስት የደገሰለትን ኢ ፍትሓዊ የጦርነት ጥሪ አልቀበልም በማለት የሚከተለዉን የቦክሰኛዉ መሓመድ ዓሊ ጥቅስ አንድ ጏደኛየ በኢሜል ልኮልኝ እኔም እጅግ ጠቃሚ ሆኖ ስላገኘሁት ላካፍላቹህ ወደድኩ።
“My conscience won’t let me go shoot my brother, or some darker people, or some poor hungry people in the mud for big powerful America. And shoot them for what? They never called me nigger, they never lynched me, they didn’t put no dogs on me, they didn’t rob me of my nationality, rape and kill my mother and father. … Shoot them for what? How can I shoot them poor people? Just take me to jail.”
********
በሆርን አፌይርስ የታተሙ የሜ/ጄ አበበ ተክለሃይማኖት ጽሑፎች፡-
10 Comments
  1. Sara
    I haven’t seen any problem with what General Samura was saying. He was tring to pass the historical background of the Tigriay people struggle. The author of the above article tried to dwarf what was said, and twist the truth. But this is my opinion.
    we need to encourage such opportunities to communicate with high rank officials.
  2. Caalaa
    Does this mean what I think it means? ” ከአስራ አምስት አመት በላይ የአገር መከላከያ ኢታማዦር ሹም ሆነው ሲያገለግሉ፣ ብዙ ጀግኖችና ብቃታቸው ያረጋገጡ ከፈተኛ መኮንኖች የነበሩት መከላከያ እሳቸው ከተነሱ አደጋ ዉስጥ የሚገባ ከሆነ እማ አስራ ኣምስት ዓመት ጥፋት ሲፈፅሙ ነበር ማለት ነው፤ እሳቸው በሌሉበት እንደ ተቛም የበለጠ ተጠናክሮ የማይሰራ ከሆነ ይች አገር በእዉነትም አደጋ ላይ ነው ያለችው።” Overall intersting observation, but please stop beating a dead horse. Derge was gone years ago, and it is not the worst arguably in our history. Also, the war between you guys and derge was, for most of us, a civil war. Nobody is really liberator or colonizer.
  3. Nigus
    bullshit from tigres. dear ethiopians, never trust agamies for love or money. they never seem to learn from their past rather they keep being arrogant. የት የነበረ ዴሞክራሲ ነው የሚጨላልመው? ቅራቅንቦህን አትዘባርቅ። አጋሜዎች ለማስመሰል ብቻ ነው ኢትዮጵያ የሚሉት። በትንሹ እንኳን ብናይ ይሄ አስመሳይ ትግሬ የቅማንትን ጉዳይ ሲያነሳ የወልቃይትን ባልሰማ ላሽ አለው። አሁን የቅማንት ጉዳይ ወቅታዊ አይደለም። እዛ አካባቢ መረጋጋት ባለበት ሁኔታ የወቅቱን አንገብጋቢ ጉዳይ የወልቃይትን የአማራነት ጥያቄ እንደሌለ አድርጎ አለፈው። እናንተን የምናምንበት ጊዜ ላይመለስ አልፏል። ዋጋችሁን የምታገኙበት ጊዜ እየገሰገሰ ቀርቧል። እዛው እራሳችሁን ቻሉ። በኢትዮጵያውያን አትመሳሰሉ። አታጎብድዱ። ለነገሩ ባንዳ ሲያጎበድድ ነው ሚያምርበት።
  4. Sasahu
    እኔ እምለው ለእነዚህ ሰዎች ሌላ ኢትዮጽያ አለቻቸው ወይስ 100 ሚሊዮን በምንሆነው እኛ በምንኖርባት ኢትዮጽያ ውስጥ ነው የሚኖሩት። የኢትዮጽያ ህዝብን ግን እንዴት ነው የምታዮት ጎበዝ? እንደናንተ ከትግል መልስ በግዢም ይሁን በተላላኪ PhD ባይኖረውም ወይም የ PhD ተማሪ ባይሆንም እኮ ኑሮ እየኖረ ነው፤ እለት ተእለት ላለፉት 25 አመታት የናንተን ዘመን እና መንግስት እኮ እየኖረው ነው። ከዚህ በላይ፣ ከህይወት ለምዱ በላይ ምን ይፈልጋል እናንተን ለማወቅ። ልቅም አርጎ እኮ ያቃችኋል። እናንተ እንደልብ ስለታናገራችሁ፣ ነጻነት ስላላችሁ (ህዝብን እንደፈለገ ለመግዛት)፣ እንደምትፈልጉት መብላት፣ መጠጣት፣ በሀብት እና በገንዘብ አናት ላይ መውጣት፣ ማዘዝ መናዘዝ ስለቻላችሁ የኢትዮጽያ ህዝብ ሁሉ እነደዛ የሆነ ስላናንተም እንደናንተ የሚያስብ ይመስላችኋል እንዴ? “ዲሞክራሲ እየጨለመ ነው” ስትል አንደበትህን ስቅጥጥ አያረገውም። ደርግን እጥፉን ተክታችሁ፣ ከኛ በላይ ላሰር ብላችሁ፣ ትናንት ደብተርና እስኪሪብቶ የያዙን ህጻናትን ባደባባይ እየረሸኑ፣ ነብሰጡር ሰወነትዋን በጥይት እንደወንፊት እየበሳሱ፤ “ዲሞክራሲ እየጨለመ ነው” የሚለውን ቃል መናገር ጉድ ነው የሚያሰኘው፣ ሌል ምን ይባለል። አብራችሁ በህዝብና በሃገር ላይ ደባ ስትሰሩ ትቆዮና ትንሽ ስታኮርፉ ለይምሰል መሞነጫጨር ፤ ለሃገር ሃሳቢም ወይም ባለእውቀት/ተማሪም አያሰኝም። ለሞሆኑ ጽሁፍህ ምን ያህል ወያኔ ወያኔ እንደሚሸት ተገንዘበኅዋል፤ እኛ እንደሚጋባን የ Ph.D. ተማሪ ሃገራዊ የሆኑ historical, social, political, and political economy ምሁሮችን እና ጽሁፎችን ከ global political economy ጉዳዮች ጋር እያጣቀሰ ትንታኒ ይሰጣል እንጂ ፤ የሞተውን ደርግ ቀስቅሶ ስለሱ የህዋሃትን ማንፊስቶ ወይም የኢህአዴግን አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊን እንደሰማው አይጽፍም። አንድ እውነት አለ፤ የምትጣሉ ወይም የተጣላችሁ እየመሰላችሁ ህዝብ አታደናግሩ እናንተ መቸም ያው ወያኔ (ህወሃት) ያው ወያኔ ናችሁ።
  5. P
    “እናንተን የምናምንበት ጊዜ ላይመለስ አልፏል። ዋጋችሁን የምታገኙበት ጊዜ እየገሰገሰ ቀርቧል። እዛው እራሳችሁን ቻሉ። በኢትዮጵያውያን አትመሳሰሉ። አታጎብድዱ። ለነገሩ ባንዳ ሲያጎበድድ ነው ሚያምርበት።” What does this mean? and to whom? Is this for the party, for the government or for the people? It is clearly stated to insult the people, and that is nonsense! AYIBALM ESHI my baby, NIGUSYE??
    Ethiopia has a history and civilization of more than 3,000 years. And you know what? With out her people, it will remain with no history!!! Just like you, a man who knows only curse and insult towards the PROUD people!
  6. Muhammed Jemal
    በመጀመሪያ ይሄን ያለዉን ሰላምና ዴሞክራሲ ላመጡልን አሁን በሂወት ያሉና ያለፉ ሰመአታት ትዉልድ የማይረሳዉ ታላቅ ገድል ፈፅማችሓልና የላቀ ምስጋና ይገባችሓል ማለት እፈልጋለሁ!! ወደፅሁፉ ስመለስ; ሀገርን የሚመራ መንግስት ለሀገር ግንባታም ሆነ ለሀገር መፈራረስ ምክኒያት ሊሆን ይችላል ስለዚህ መንግስት እራሱን በሚገባ መፈተሽ ይኖርበታል እላለሁ! ሌላዉ ማለት እምፈልገዉ ነገር እኛ ኢትዮጵያኖች አስተዋዮች እና ብልሆችነን ሰለዚህ ይህንን ባህሪያችን ለማስቀጠል ከተፈለገ የብልህ አይምሮና የአስተዋይነት ማኖቆ የሆኑትን ብሄርተኝነት;ጎጠኝነትና ጭፍን ጥላቻነረ ከመጡበት ጉድጓድ መልሰን መቅበር መቻል አለብን. በመጨረሻም ይሄን ትንታኔ ፅሁፍ ላቀረቡልን ለሜ/ጄ አበበ ተክለሃይማኖት ከፍተኛ መስጋና ማቅረብ እፈልጋለሁ!
  7. fuck you
    ቢላዋ ሲሳል የሰማች ዶሮ፡ ቁቅ ቁቅ ማለትዋ ስለቱ የተዘጋጀው ለኔ ነው ማለትዋ ነው፡፡ ዛሬ በፅሁፍ መላላጣችሁና መናቆር፡ ኮሮምቦላ ድንጋይ ስትይዙና ዊስኪ ስትጨልጡ የሚንር፡ ሃንጎቨራችሁ አብቅቶ ጠዋት ከሴት ብሽሽት ስር ስትወጡ ደግሞ የሚቀር መሆኑን ሕዝቡ ያውቃል፡፡ የቦዘኔና ቀምቶ አደር ፀብ ክፍፍል ላይ ነው፡፡ የሚገርመኝ ግን የፈለጋችሁትን ያህል ብትዘርፉ ብስባሾች መሆናችሁን መርሳታችሁ ነው፡፡
  8. Jayce
    Hill curried a lot of favor with the Hurleys when RU played [and lost to] St. Peter’s at the refurbished Jersey City Armory last November. The Armory is run by the Jersey City Recreation Department. Guess who is in charge of the Rec Dept.? Bob Hurley.SHU had a chance to play that &#2pn6;re-o8eni1g’ game but hemmed and hawed and ultimately decided not to play St. Peter’s there until the 08-09 season.

2017 ሜይ 23, ማክሰኞ

በሳዑዲ በኢትዮጵያውያኑ ላይ የትናንቱ እንዳይደገም

tg

        በሳዑዲ በኢትዮጵያውያኑ ላይ የትናንቱ እንዳይደገም

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2009 (ኤፍ ቢ ሲ) በአረብ ሀገራት ኢትዮጵያውያን በብዛት ከሚኖሩባቸው ሀገራት አንዷ ሳዑዲ አረቢያ ናት።
በሀገሪቱ በየአመቱ የሚካሄዱ ሃይማኖታዊ ስነስርአቶችን ጨምሮ በልዩ ልዩ መንገዶች ወደ ሀገሪቱ የሚገቡ ዜጎች በህጋዊም ሆነ የሀገሪቱን ህግ ተላልፈው ለአመታት ሲኖሩባት የቆችው ይህቺ ሀገር፥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በውጭ ሀገራት ዜጎች ዙሪያ ጠንካራ ህጎችን በማውጣት እርምጃ እየወሰደች የምትገኝ ሀገር ሆናለች። እንደ ሌሎች ሀገራት የውጭ ዜጎች በልዩ ልዩ የስደት ሰበቦች በሀገሪቱ ለመኖር ቢፈልጉ ይህንን የሚያስተናግድ ህግ የላትም። በአብዛኛው ከተለያዩ ሀገራት ወደ ሀገሪቱ የገቡ የውጭ ዜጎች ይኖሩባታል።
ኢኮኖሚዋ ከነዳጅ በሚገኝ ገቢ ላይ የተመሰረተው ይህች አገር የምርቱ በዓለም ገበያ ላይ ዋጋው እየወረደ መምጣት ፈተና ሆኖባታል። ይህንን ተፅእኖ ለመቋቋም የመንግስት የወጪ ቅነሳን የሚያበረታቱ የኢኮኖሚ ማሻሻያዎችን አዘጋጅታ በመተግበር ላይ የምትገኝ ሲሆን፥ ስራ አጥ ለሆኑ የአገሬው ሰዎች የስራ እድልን ያመጣሉ ያለቻቸውን እርምጃዎችንም ስትወስድ ቆይታለች። ከእነዚህ እርምጃዎች መካከል በተለይም በአገልግሎት ዘርፎች ላይ የሚገኙ ስራዎች ያለ አግባብ በውጭ አገራት ዜጎች ተይዘዋልና እነዚህን የስራ እድሎች ለሳዑዲ ዜጎች ክፍት ሊደረጉ ይገባል ይላሉ ፖለቲከኞቿ። ይህ እንዲሆን ህጋዊ ሰነድ የሌላቸውን የተለያዩ አገራት ዜጎች ከግዛቷ ማስወጣትን እንደ አንድ አማራጭ በመያዝ በተለያዩ ጊዜ በዘመቻ ስታስወጣ ቆይታለች።
በዚሁ ዙሪያ የሳዑዲ አረቢያ መንግስት እ.ኤ.አ ከ2013 ጀምሮ አንድ ጠንከር ያለ ህግ ደነገገ። በዚህም ህግ በሀገሪቱ የሚኖሩ የማንኛውም ሀገር ዜጎች ከሀገሪቱ በሰባት ወራት ጊዜ ውስጥ እንዲወጡ አዛለች። ዘንድሮም መሰል ህግን አገሪቱ አውጥታለች። በቅርቡ የወጣው የምህረት አዋጅ ደግሞ በዚያች አገር ለመኖር የሚያስችላቸው ህጋዊ ሰነድ የሌላቸው የሌሎች አገራት ዜጎች በ90 ቀናት ውስጥ ሀገሪቱን ለቀው እንዲወጡ ያዛል።
በአውሮፓውያኑ 2013 የሳዑዲ አረቢያ መንግስት በሰጠው የሰባት ወራት የይቅርታ ጊዜ ውስጥ ሀገሪቱን ለቀው የማይወጡ ከሆነ በሃይል እንደሚያስወጣ መንግስት በተደጋጋሚ አስታውቆ ነበር። በዚያን ጊዜ የኢትዮጵያ መንግስት ይህንን ክስተት በዜጎች ህይወት እና በባዕድ ሀገር ያፈሩት ንብረት ላይ ጉዳት እንዳይደርስ ጥረት በማድረጉ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ወደ ሀገራቸው በሰላም እንዲመለሱ አድርጓል።

በርካታ ዜጎች ግን የምህረት አዋጁን ባለመጠቀማቸው የሳዑዲ መንግስት የቀሩትን ቤት ለቤት አሰሳ ባማካሄድ ህጋዊ ሰነድ አልባ ዜጎችን በቁጥጥር ስር በማዋል ከአገር እንዲወጡ አደርጓል። በዚሁ ሂደት በኢትዮጵያውያኑ እና በሀገሪቱ ፖሊሶች መካከል በተደረጉ ግጭቶች ብዙዎቹ ለሃይል ጥቃት የተዳረጉ እና ሶስት ሰዎችም በእነዚሁ ግጭቶች ሳቢያ ለሞት መዳረጋቸው በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ሲዘገብ ነበር።

እንደ ሚድል ኢስት ዘገባ ከአራት አመት በፊት ሳዑዲያ አረቢያ ባወጣችው የምህረት አዋጅ ጊዜ ከተጠናቀቀ በኋላ አሰቃቂ ድርጊቶች ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ በተለያዩ ሀገራት ዜጎች ላይ ተፈፅመዋል። በአብዛኛዎቹ ኢትዮጵያውያን ላይ ይደርስ የነበረው እንግልት፣ የአካል ቅጣት እና ሞት መንግስት ባደረገው ከፍተኛ ጥረት እንዳይደርስባቸው ማድረግ ቢቻልም ፤ የጉዳዩን አሳሳቢነት ቸል ባሉ ጥቂት የማይባሉ ኢትዮጵያውያን ላይ ደግሞ ከፍተኛ ችግር እንዲደርስባቸው መሆኑ አሳዛኝ ክስተት እንደነበር ማስታወስ ይገባናል።
በወቅቱ የአለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋማት ባወጡት ሪፖርቶች የምህረት አዋጁ ከተጠናቀቀ በኋላ የምህረት ጊዜውን ያላከበሩ የሁሉም ሀገር ዜጎች ለእንግልት፣ ለእስር፣ ለድብደባ እና ለሞት መዳረጋቸውን ያነሳሉ።
የሳዑዲ አረቢያ ፖሊሶች ቤት ለቤት ባደረጉት አሰሳ የሀገሪቱን ህግ የተላለፉ እና በህገወጥ መንገድ ያለምንም የጎዙ ሰነድ እና የስራ ፍቃድ በሀገሪቱ የሚኖሩ ኢትዮጵያንን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራት ዜጎችን ሃይል በተቀላቀለበት ድርጊት በካምፕ በማሰር እና ከፍተኛ የአካል እና የስነልቦና ጥቃቶች ማድረሳቸው አይዘነጋም። የምህረት ጊዜው እንደቀላል አይተውት ያለፉት ኢትዮጵያውያን በሃይል ከሀገሪቱ መውጣት አልቀረላቸውም። ለፍተው ያፈሩት ጥሪትም በልዩ ልዩ መንገዶች ባክነዋል። የምህረት ጊዜውን ሳይጠቀሙ በመቅረታቸው በሳዑዲ አረቢያ ፖሊስ ተይዘው ያፈረቱን ሀብት በአግባቡ ሳይዙ ተዋክበው ወደ አገራቸው እንዲመለሱ የተደረጉ ኢትዮጵያውያን ቁጥር ከ100 ሺህ ይልቃል።
ሳዑዲ አረቢያ እንደ አደጉ ሀገራት የስደተኛ መብት የሚያስጠብቅ ስርአት ባለመኖሩ፥ በፍርድ ቤት ተከራክሮ መብትን ማስከበር የማይታሰብ ነው። የምህረት አዋጅ ጊዜ ካበቃ በኋላ ደግሞ ለህግ አስከባሪዎች የሚሠጠው ስልጣን ገደብ የሌለው በመሆኑ የሰብአዊ መብቶች ይከበራሉ ብሎ መጠበቅም የዋህነት ነው። በአሁኑ ወቅት ሀገሪቱ የሰጠችውን የምህረት ጊዜ በልተጠቀመ የየትኛውም የውጭ ሀገር ዜጋ ላይ እርምጃ እወስደላሁ እያለች ነው። ይህንን ተፈጻሚ እንደምታደረግ ከዚህ በፊት ያደረገችው ድረጊት ማስታወስ ይበቃል። የአሁኑ ደግሞ የባሰ እንደሚሆን መገመት አይከብድም።
እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር ከህዳር 4/2013 ጀምሮ የሳዑዲ አረቢያ ፖሊስ እና የሰራተኞች ሚኒስቴር ባለስልጣናት ሀገር አቀፍ ዘመቻ በማካሄድ ሰደተኞችን በማሰስ፣ በማሰር እና ህጋዊ ሰነድ የሌላቸውን የውጭ ሀገራት ሰራተኞች ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ አድርገዋል። በሚያዚያ 2013 ደግሞ የሰራተኛ ህግ አንቀጾች ህጉን በማሻሻል ሰነድ አልባ የውጭ ሀገር ሰራተኞች በማሰር እና በሃይል ከሀገር የማስወጣት ተግባር ጠንካራ እንዲሆን አድርገው ነበር።
በወቅቱ በሳዑዲ አረቢያ የተካሄደው ዘመቻ በየሰፈሩ እና በገበያ ስፍራዎች እንዲሁም በልዩ ልዩ የፍተሸ ጣቢያዎች መታወቂያ በመጠየቅ ሲሆን፥ በሁለት ቀናት ብቻ 20 ሺህ ሰራተኞችን እንዳሰረች መረጃዎች ያስረዳሉ። በ2104 ከመላው ሀገሪቱ 427 ሺህ የመኖሪያ ፍቃድ የሌላቸው ተለያዩ ሀገራት ዜጎችን ከሀገር ማስወጣቷን ሪፖርቶች ይገልፃሉ። በውቅቱ የአረብ ኒውስ እንደዘገበው፥ 108 ሺህ 345 ሰደተኛ ሰራተኞችን በማሰር 90 ሺህ 450 የሚሆኑትን በ40 ቀናት ውስጥ ወደ ሀገራቸው በግዴታ መልሳለች። እ.ኤ.አ በ2017 መጋቢት ወር ጀምሮ ባሉት አምስት ወራት ደግሞ 300 ሺህ የውጭ ሰራተኞችን ያባረረች ሲሆን፥ ይህም በአማካይ በቀን 2 ሺህ ሰዎችን በሃይል ወደ መጡበት መልሳለች ማለት ነው።
የሳዑዲ አረቢያ ንጉስ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ስብሰባ ላይ ባደረጉት ንግግር ሀገራቸውም በምንም ሁኔታ ህገወጥ የሰዎች ዝውውር እንደማትታገስ እና የመኖሪያ ፍቃድ ሳይኖራቸው በሀገሯ የሚኖሩ የውጭ ዜጎችን በምንም ምክንያት በሀገሯ እንደማይኖሩ በጽኑ ተናግረዋል። ይህን አቋሟም በሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ድረ-ገጽ ላይ ሰፍሯል።
ከሶስት አመት በፊት ሳዑዲ አረቢያ ያወጣችውን ህግ ያላከበሩ ስደተኞች ባከሄደቸው ዘመቻ ሰነድ አልባ የሆኑ የውጭ ሀገር ሰራተኞችን ሀይል በተቀላቀለበት ሁኔታ ወደ እስር ቤት ካምፖች እንዲገቡ ማድረጓን ተከትሎ አለም አቀፍ ተቋማት ባደረጉት ፍተሸ ኢትዮጵውያንን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራት ዜጎች ላይ የሃይል ጥቃት መድረሱን ይገልጻሉ። በወቅቱ ኢትዮጵያው በብዛት የሚኖሩበት ደቡባዊ ሪያድ በሚገኘው ማንፉሃ በተሰኘ መንደር በፖሊስ እና በኢትዮጵውያን መካከል በተቀሰቀሰ ግጭት ቢያንስ ሶስት ሰዎች የሞቱ ሲሆን፥ በርካቶች ደግሞ አካላቸው ላይ ጉዳት እና ያፈሩት ጥሪት እንዲያጡ ሆኗል።

የሳዑዲ አረቢያ መንግስት የሀገሪቱን ህግ የተላለፉ የውጭ ሀገር ዜጎች ያለምንም እስራት እና የገንዘብ ቅጣት ሀገሪቱን ለቀው እንዲወጡ አዲስ የምህረት አዋጅ ማውጣቱ ይታወቃል። የምህረት አዋጁ ከመጋቢት 20 ቀን 2009 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ እየተደረገ የሚገኝ እና ለ90 ቀናት የሚቆይ እንደሆነ በተደጋጋሚ ተገልጿል።
በህግ የሚፈለጉ፣ የፍርድ ቤት ጉዳያቸውን ያልጨረሱ ግለሰቦች እና በእስር ቤት የሚገኙ የህግ ታራሚዎች ጉዳይ በምህረት አዋጁ አልተካተተም።
በአዲሱ የሳዑዲ ህግ ውስጥ ከተካተቱ ዋና ዋና ነጥቦችም
  • የሳዑዲን ህግ የተላለፉ የውጭ ሀገር ዜጎች ያለምንም ቅጣት በ90 ቀናት ሀገሪቱን ለቀው እንዲወጡ ሲያስቀምጥ ህጋዊ ማዕቀፉን ተከትለው ወደ ሳዑዲ ዓረቢያ መመለስ የሚፈልጉ የሚመለሱበትን አማራጭ አስቀምጧል። 
  • በህግ የሚፈለጉ፣ የፍርድ ቤት ጉዳያቸውን ያልጨረሱ ግለሰቦች እና በእስር ቤት የሚገኙ የህግ ታራሚዎች ጉዳይ በ2017 የምህረት አዋጅ አልተካተተም፤ እንደነዚህ አይነት ጉዳዮች ተለይተው በሀገሪቱ ህግ እንደሚስተናገዱ ተገልጿል።
  • በህግ የሚፈለጉ እና የህግ ሂደታቸውን ያልጨረሱ ግለሰቦች ጉዳያቸው በሚመለከታቸው የፖሊስ ተቋማት ተጣርቶ የሚቀርብ ይሆናል።
  • ህጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ (ኢቃማ) ያላቸው ዜጎች የ2017 የምህረት አዋጅ አይመለከታቸውም የሚሉት ይገኙበታል።
የሳዑዲ አረቢያ መንግስት ያለ ህጋዊ የመኖሪያ እና የስራ ፈቃድ የሚኖሩ የማንኛውም ሀገር ዜጎች በ90 ቀናት ውስጥ ከሀገሪቱ እንዲወጡ ማሳሰቡን ተከትሎ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ልኡካኑ ቡድን ወደ ሳዑዲ አረቢያ አቅንቶ ነበር።
የኢትዮጵያ መንግስት የሳዑዲ አረቢያን ህግ ተላልፈው በሀገሪቱ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ሳይጉላሉ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ለማድረግ ከሳዑዲ ባለስልጣናት ጋር የሚመክር እና አቅጠጫ የሚያስቀምጥ የልኡካን ቡድን ወደ ሪያድ በመሄድ በሁኔታው ዙሪያ ወይይት አድርጓል። የኢትዮጵያ መንግስት ዜጎቹ ያለመጉላላት ወደ ሃገራቸው በሰላም እንዲመለሱ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት አድርጓል።
በአሁን ወቅትም በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኩል አስተባባሪ ኮማንድ ፖስት የተቋቋመ ሲሆን፥ በሀገር አቀፍ ደረጃም ስራውን የሚመራ ግብረ ሃይል መቋቋሙን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እየገለጸ ይገኛል።

በዚህ መልኩም በሪያድ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ እና ጅዳ ባለው ቆንጽላ ጽህፈት ቤት አማካኘነት ለዜጎች አስፈላጊውን መረጃ በማቅረብ ድጋፍ በማድረግ ዜጎች በሰላም ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ጥረት እደረገ ነው። ይህንኑ የመንግስት ማሳሰቢያ ሰምተው ወደ ሀገራቸው እየተመለሱ ቢሆንም፥ ህጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ ሳይኖራቸው በዚያች አገር ከሚኖሩ አስከ 300 ሺህ የሚደርስ ኢትዮጵያውያን መካከል በይቅርታ ጊዜው ለመጠቀም የጉዞ ሰነድ የወሰዱት ዜጎች ቁጥር 23 ሺህ ገደማ ብቻ መሆኑ እንዳሳሰበው መንግስት በተደጋጋሚ በመግለፅ ላይ ይገኛል።
ሚኒስቴሩ በመንግስት በኩል እስከ 90 ቀናት ወደ ሃገራቸው ለሚመለሱ ዜጎች ወደ የመጡበት አካባቢ የሚመለሱበትና ቀጣይ ህይወታቸውን የሚመሩበት ሁኔታ ላይ ከዚህ ቀደም እንደተደረገው መንግስት አስፈላጊውን ሁኔታ እንደሚመቻች አስታወቋል።
በባእድ ሀገር ለፈተው ያፈሯቸው ንብረቶቻቸው በቀረጥ ሳቢያ ችግር እንዳይገጥማቸውም መንግስት ከቀረጥ ነጻ እንዲያስገቡ የፈቀደ ሲሆን፥ መንግስታዊ እና መንግሰታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ተመላሾቹን በሚገባ ለማደራጀት እና ቀጣይ ህይወታቸውን የሚመሩበት ብርቱ ድጋፍ እንደሚያደረጉ ቃል ገብተዋል።
በዚህ ሁሉ ጥረት መሃል በሳዑዲ አረቢያ መንግስት የተሰጠው የምህረት አዋጅ እና ቀነ ገደብ ግን በዚያች ሃገር በሚገኙ እና ወደ ሃገራቸው በተመለሱ ኢትዮጵያውያን ዘንድ የተደበላለቀ ስሜት መኖሩን ሰሞኑን ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ባናገራቸው አስተያየት ሰጪዎች ዘንድ ተስተውሏል።
ከአመታት ቆይታ በኋላ በአዋጁ ምክንያት ወደ ሃገሯ የተመለሰችው ወጣት መስተዋት ሃገሯ ብትገባም የሌሎችን መመለስ ግን አትደግፍም ።
እንደ እርሷ ገለጻ ዓረብ ሃገር ፈተናው የበዛ ቢሆንም ሄዶ ስራ መስራት ያስፈልጋልና ዛሬ ብትመለስም ወደዛው ስለመመለስ እንደምታስብ ትናገራለች።
ከመስታወት ጋር ወደ ሃገሯ የተመለሰችው ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት ደግሞ ከጓደኛዋ በተቃራኒው በዚያች ሃገር መቆየት ካለው ፈተና አንጻር የማይመከር ነው ትላለች።
ከአራት ዓመት በፊት በሳዑዲ እስር ቤት ከርሞ ወደ ሀገሩ የተመለሰው ሌላኛው ኢትዮጵያዊ ሃብቶም ደግሞ፥ ዓመታት ለፍቶ ያፈራውን ንብረት እዚያው ትቶ ወደ ሃገሩ መግባቱን ያስታውሳል።
ይህ የእርሱ እጣ ፋንታ በሌሎች የሃገሩ ልጆች ላይ እንዳይደርስም አዋጁን ተጠቅመው እንዲወጡ ይመክራል።
የሳዑዲ አረቢያ መንግስት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሰብሰባ ላይ የመኖሪያ ፈቃድ አልባ የሌሎች አገራት ዜጎችን በለማስወጣት ያለውን ጽኑ አቋሙ ይፋ አድርጓል። በመሆኑም በአውሮፓውያኑ 2013 ላይ የይቅርታ ጊዜውን ተጠቅመው ባልወጡ ኢትዮጵያውያን ላይ የደረሰው ዘንድሮ እንዳይደገም ሁሉም ወገን የበኩሉን ሚና እንዲጫወት መንግስት መጎትጎቱን ቀጥሏል። የከፋ ሁኔታ ሲፈጠር የዜጎችን ጉዳት ለማህበራዊ ገፆች ፍጆታ ከመጠቀም ይልቅ አሁን ላይ እነዚህን ገፆችንም ሆነ ሌሎች መንገዶችን ተጠቅሞ ኢትዮጵያውያኑ የይቅርታ ጊዜውን እንዲጠቀሙ እና ሊመጣ ከሚችለው ጥቃት እንዲድኑ ማሳሰብ ለሁሉም ይበጃል።
በጋዜጠኛ ተክለሃይማኖት ገብረመድህን
ባህር ዳር